Tuesday, July 3, 2018
🍃_____ የሺዓ ሐይማኖት _____ 🍃
......... ክፍል አራት (4)....
ምስጋና ሁሉ ለአሏህ ይገባው፡፡ በመልዕክተኛው ሰለሏሁ አለይሒ ወሰለም ላይ የአሏህ ረድኤት ሶላት ዘወትር ይውረድ፡፡ አልሐምዱሊላህ ወደዚህ ኢስላም አሏህ ባይመራን ኖሮ እኛ የተመራን አንሆንም ነበር፡፡
በዛሬም አጭር ትምህርት የሺዓ ሐይማኖት ተከታዮች የሙስሊሞችን መንገድና ዲን የተቃረኑበትን ነጥብ በመጠኑ ለማየት እንሞክራለን፡፡
በመጀመርያ እነዚህ የኢስላምና የሶሐቦች ጠላቶች " በሱና ላይ ያላቸው እምነት ምን እንደሚመስል " እንከታተል፡፡
እነዚህ ሺዓዎች በግልፅ የነብዩ ሰለሏሁ አለይሒ ወሰለም ሐዲስን ወይም ሱናን የሚዋጉ ናቸው፡፡ ለዚህም ነው አህሉ ሱናዎች የሚለው ስያሜ የነሱ ልዩ የሆነ መጠረያ የሆነው፡፡ ምክንያቱም የረሱልን ሰዐወ ሱና የሚከተሉ ናቸውና፡፡
ሺዓዎች ከአንዳንድ አኢማዎቻቸው እንደሚዘግቡት እንዲህ ይላሉ ፦
أن كل شيء مردود إلى الكتاب والسنة وكل حديث لا يوافق كتاب الله فهو زخرف... ( البهبودي / صحيح الكافي ١/١١)
《ሁሉም ነገር ወደ አሏህ ኪታብና ወደ ሱና ተመላሽ ነው፡፡ እያንዳንዱ ከአሏህ ኪታብ የማይገጥም የሆነ ሐዲስ የተጌጠ ቅጥፈት ነው፡፡》
📚 ሶሒህ አልካፊ : 1/11
እንደዚህ አይነት ሌሎችም ንግግሮቻቸው አላቸው፡፡ ይህ ንግግራቸው የሚያስጠቅመን ነገር ቢኖር ሺዓዎች የነብያችንን ሰለሏሁ አለይሒ ወሰለም ሱና እንደማይቃወሙ ነው፡፡ በርግጥ ይህ ማጭበርበርያቸው ነው፡፡ እነሱ ከኢስላም ከሱና እጅ የራቁ ናቸው፡፡ አብዛኛው የኃይማኖታቸውም ምንጭ ኢማሞቻችን ብለው ከሚጠቅሷቸው 12 መሪዎቻቸው የሚወጡ አይደሉም፡፡
------- የኢማምን (እነሱ አማም የሚሏቸውን ነው፡፡ ) ንግግር እንደአሏህ ና እንደ ሩሱል ንግግር ነው ማለታቸው -------
ሺዓዎች ዘንድ ሱና ነው ብለው የሚያምኑትን እንዲህ ይገልፁታል፦
فالسنة هي كل ما يصدر عن المعصوم من قول أو فعل أو تقرير.
📚 الأصول العامة للففه المقارن ص: ١٢٢
" ከመዕሱም (ከስህተት ፍፁም የጠራ) ከሆነ ( ሰው) የሚመነጭ እያንዳንዱ ንግግር ፥ ወይም ተግባር ወይም ደግሞ ያፀደቀው ( تقرير) ነው ሱና የሚባለው፡፡ " ይላሉ፡፡
📚 ዑሉል አማ ሊልፊቅሒ አልሙቃረን ፡ 122
የነዚህ ቡድኖች የመዝሐባቸውን ብሉሽነት ላልተረዳ ሰው ፥ ወይም አህለል በይት ይወዳሉ በሚል ማታለያ የተታለለ ሰው በዚህ ንግግራቸው የተደበቀውን መርዝ በሚገባ ሊያውቀው አይችልም፡፡ ምክንያቱም እኛ ሙስሊሞች መዕሱም (ከስህተት የተጠበቁ) ስንል ከልበወለድ የማይናገሩትና በወህይ የሚናገሩትን ነብያችንን ነው የምንፈልግበት፡፡
ነገር ግን ሺዓዎች ዘንድ ይህን ባህሪይ የሚያጎናፅፉት ከረሱላችን (ሰዐወ) ውጭ ለሆነ አካል ነው፡፡ ንግግራቸው እንደአሏህና መልዕክተኛው ንግግር ነው የተባለላቸው ረሱል (ሰዐወ) ሳይሆኑ እነሱ አስራ ሁለት ( ኢማሞቻችን ) ብለው የሚጠሯቸውን ነው፡፡
ሺዓዎች ዘንድ በወህይ እንጂ ከማናገሩት ነብያችንን (ሰዐወ) እና በአስራ ሁለቱ ኢማሞቻቸው መካከል ልዩነት ያደርጉም፡፡ አንዳንዴ አኢማዎች ከሌሎች ነብያት የበለጡ ናቸው እስከማለትም ይደርሳሉ፡፡
ኢማሞቻቸው የማይሳሳቱ ፥ የማይረሱ ፥ የማይዘናጉ ፥ ወንጀል የማይሰሩ ...ወዘተ እያሉ ድንበር እያለፉ ኢስላምን ይሞግታሉ፡፡ በዚህ ዘመን ካሉ አለቆቻቸው አንዱ እንደሚሞግተው
" በእነዚህ አኢማዎች ጥቡቅነት ማመን ከነሱ የሚመንጭ ንግግር ሁሉ ሶሂህ ማድረግ ነው፡፡ ሰነዱ ወደ ነብያችን ሰዐወ መድረሱ መስፈርት ሳይደረግ ፡፡ ልክ በአህሉ ሱና እንደሚባለው፡፡ " ( ሙሐመድ ሪዷ አልሙዘፈር)
- እነዚህ ሺዓዎች ዘንድ አኢማዎች ማለት ልክ እንደ ረሱል (የአሏህ መልዕክተኛ) አድርገው ነው የሚቆጥሩት ፡፡ በታዓምራት በተለያዩ ነገሮች ከአንቢያዎች እንደሚስተካከሉ ይሞግታሉ፡፡ እንዲህም ይላሉ ፦
《قولهم قول الله ، وأمرهم أمر الله ، وطاعتهم طاعة الله. ومعصيتهم معصية الله ، وإنهم لم ينطقوا إلا عن الله تعالى وعن وحيه.》
📚 ابن بابويه / الاعتقادات ص :١٠٦
" (የአኢማዎች) ንግግራቸው ፥ የአሏህ ንግግር ነው፡፡ ትዕዛዛቸው የአሏህ ትዕዛዝ ነው፡፡ እነሱን መታዘዝ አሏህን መታዘዝ ነው፡፡ እነሱን ማመፅ አሏህን ማመፅ ነው፡፡ እነሱ ከአሏህ ዘንድ በሆነ ወህይ እንጂ አይናገሩም፡፡ "
📚 አልኢዕቲቃዳት ፡ 106
ይህ ነው እንግዲ የሺዓ ሐይማኖት የሚባለው፡፡
አልካፊ የሚባል እጅግ የሚመረኮዙበት ኪታብ አላቸው፡፡ በዛ መፅሐፍ እንደዘገቡት እንዲህ ብሏል ፦
የአቡ ዐብድሏህ ንግግር ነው ብለው ይሞግታሉ ፦
" የኔ ሐዲስ የአባቴ ሐዲስ ነው፡፡ የአባቴ ሐዲስ የአያቴ ሐዲስ ነው፡፡ የአያቴ ሐዲስ የሑሰይን ሐዲስ ነው፡፡ የሑሰይን ሐዲስ የሐሰን ሐዲስ ነው፡፡ የሐሰን ሐዲስ የአሚረል ሙእሚኒን ሐዲስ ነው፡፡ የአሚረል ሙእሚኒን ሐዲስ የረሱል (ሰዐወ) ሐዲስ ነው፡፡ የረሱል (ሰዐወ) ሐዲስ ደግሞ የአሏህ ዐዘ ወጀል ንግግር ነው፡፡ "
📚 ዑሱል አልካፊ ፡ 1/53 ኪታብ ፈድሉል ዒልም
የዚህ ኪታብ ሸርህ ባለቤት ሲናገር በዚህ ማስረጃ አማክኝነት የአኢማዎች ንግግር ሁሉ የአሏህ ንግግር ነው ማለት ነው፡፡ በንግግራቸው ምንም አይነት መጋጨት የለበትም፡፡ ልክ በአሏህ ንግግር መጋጨት እንደሌለው ሁሉ፡፡
📚 ሸርህ ጃሚዕ አለል ካፊ ፡ 2/272
ከነዚህ ከሚያስቀምጧቸው መሠረቶች ተነስተን እነዚህ ጭፍራዎች በዓሊይ (ረ.ዓ) ላይ ወይም በልጆቹ አልፎ በአሏህ ላይ መቅጠፍና መዋሸት ቀላል ነገር አድርገው ዲን ብለው እንደያዙት ነው፡፡ ሐሰን የተናገረው ዓሊይ ብሎታል ተብሎ ሊወራ ነው፡፡ አዑዙቢላህ...
የአልካፊ ሸርህ ባለቤትም የአኢማዎች ንግግር ወደ አሏህ አስጠግቶ ማውረት የተሻለ መሆኑ ገልፇል፡፡ ይህ ትልቅ ዙልምና በአሏህ ላይ ወሰን ማለፍ ነው፡፡
-በቀጣይ ሌሎችም የዚህ መጁስ የሆነ የኩፍር ቡድን ጥመቶችና መንገዳቸው በአጭር አጭሩ እንመለከታለን፡፡
አስቀድሞ ነው እንጂ .... መደቆስ
አሁን ምን ያደርጋል ድስጥ ጥዶ ማልቀስ
እንዳይሆን ከአሁኑኑ መጠንቀቅ ነው፡፡
☞ወቢላሒ አትተውፊቅ
📮 አቡ ኀኒዕ ናሙስ
📮 ረጀብ 28 1439 ዓ.ሒ
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
የኢብኑ ተይሚያህ አቋም በተሃኩም ላይ...
፨ በአሏህ ሥም እጅግ በጣም አዛኝና በጣም ሩህሩህ በሆነው እጀምራለሁ፡፡ ፨ በዚህ ፅሁፍ ሼይኹል ኢሥላም ኢብኑ ተይሚያህን ከኸዋሪጆች አመለካከት እናጠራለን፡፡ አቡ ኢምራን ብዙዎች እንደምታውቁት ሁለት ገሪብ የኸዋሪጆችን...
-
🔖 በአሏህ ሥም እጅግ በጣም ሩህሩህና እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው እጀምራለሁ፡፡ በዚህ ሁፍ በአሏህ እርዳታ በመታገዝ ወደ ጧጉት መፋረድ ምን እንደሆነ እና ወደ ጧጉትም መፋረድ ያለው ሁክም እንመለከታለን፡፡ በምን አይነት...
-
✔ በአሏህ ስም እጅግ በጣም አዛኝና ሩህሩህ በሆነው እጀምራለሁ፡፡ الحمد لله وصلاة وسلام على رسول الله وعلى آله وصحبه ومن والاه ..... أما بعد ° በዚህ አጠር ያለ ትምህርት ...
-
📌 [ አል-መድኸሉ ኢላ አልጃሚዕ ፊ ኩትቢ አል ኢማን ወርረድ ዓለል ሙርጂአህ ] -------------- ክፍል _ 2 -------------- بسم الله الحمد لله والصلاة والسلام على رسول ...
No comments:
Post a Comment