Thursday, September 17, 2020

የኢብኑ ተይሚያህ አቋም በተሃኩም ላይ...

 

፨ በአሏህ ሥም እጅግ በጣም አዛኝና በጣም ሩህሩህ በሆነው እጀምራለሁ፡፡

፨ በዚህ ፅሁፍ ሼይኹል ኢሥላም ኢብኑ ተይሚያህን ከኸዋሪጆች አመለካከት እናጠራለን፡፡ አቡ ኢምራን ብዙዎች እንደምታውቁት ሁለት ገሪብ የኸዋሪጆችን ሹብሃ ሲረጭ እናውቀዋለን፡፡

1). "በአሏህ ሸሪዐ መፍረድ የተወ ሁሉ ይከፍራል" ይላል፡፡
2). "ሙሽሪኮችን መታዘዝ ያለምንም ገበድ (ማለትም ኢስቲህላል ሳይኖርበት) ትልቁ ሽርክ ነው ያከፍራል" ይላል፡፡

እነዚህ ባጢል አመለካከቶች በሼይኹል ኢስላም ላይ ከተናገረው ጋር አገናኝተን መልስ እንሠጣለን፡፡

በዚያ ፅሁፍ ላይ እኔ የሡን ኸዋሪጅነት እንደምገልፅ መናገሬና ያንንም አለማድረጌ ወቅሶኛል፡፡ በርግጥም በርካታ ቦታዎች ላይ የኸዋሪጆች ቢድዐ ደም ሥሩ ገብቶ ናላው እያዞረው እንደሆነ አስረድቼዋለሁ፡፡ አዎ! የኸዋሪጆች መንገድ ይዣለሁ ብሎ እስኪመሠክር አልጠብቀውም፡፡

አሁን ወደ ኢብኑ ተይሚያህ ንግግር እንሂድ፡፡ እኔ የጠቀስኩት የኢብኑ ተይሚያህ አጭር ንግግሩን ለቦታው የሚገጥም ስለነበር እንጂ ሠፋ ያለውን ንግግሩን ለማምጣት አለመፈለጌ አይደለም፡፡ እንደውም ከተባለ ከተባለ አቡ ኢምራን እጅግ ወሳኝ የሆነ የኢብኑ ተይሚያህ ንግግር ዘሎታል፡፡ እኔ እንዲህ ላስቀምጠው...
قال ابن تيمية

[ولا ريب أن من لم يعتقد وجوب الحكم بما أنزل الله على رسوله فهو كافر، فمن استخل أن يحكم بين الناس بما يراه عو عدلا من غير اتباع لما أنزل الله فهو كافر. فإنه ما من أمة الا وهي تأمر بالحكم بالعدل وقد يكون العدل في دينها ما راه أكابرهم،  بل كثير من المنتسبين إلى الإسلام يحكمون بعاداتهم التي لم ينزلها الله سبحانه وتعالى ، كسوالف البادية وكأوامر المطاعين فيهم ، ويرون أن هذا هو الذي ينبغي الحكم به دون الكتاب والسنة وهذا هو الكفر]
<< አሏህ በረሡል ላይ ባወረደው ህግ መፍረድ ግዴታ አይደለም ብሎ #የሚያምን ሠው እሱ ካፊር ነው፡፡ በሠዎች መካከል አሏህ ያወረደውን (ህግ) ሳይከተል እሱ ፍትህ ብሎ ባሰበው ነገር መፍረድን #ሃላል_ያደረገ ሠው እሱ ካፊር ነው፡፡ ነገሩ እኮ አንድም ኡማህ የለም በፍትህ መፍረድ የምታዝ ቢሆን እንጂ፡፡ በርግጥ በዲኗ ላይ ፍትህ የሚሉት ነገር አለቆቻቸው የተመለከቱ (ይሆናል ያሉት) ነገር ነው የሚሆነው ፡፡ እንደውም ብዙ ራሳቸውን ወደኢስላም የሚያስጠጉ ሠዎች አሏህ ያላወረደው በሆነ ልማዳቸው ነው የሚፈርዱት፡፡ ለምሳሌ የገጠር ሠዎች የቆየ ባህላቸው በነሱ መካከል ያሉ የሚታዘዟቸው ሠዎች ትእዛዛት ይመሥል፡፡ ይህ ነገር ከአሏህ ኪታብና ሡና ውጪ ሊፈረድበት የሚገባ ነው ብለው ያምናሉ፡፡ >>

[ فإن كثيرا من الناس #أسلموا ، ولكن مع هذا لا يحكمون إلا بالعادات الجارية لهم التي يأمر بها المطاعون ، فهؤلاء إذا عرفوا أنه لا يجوز الحكم إلا بما أنزل الله فلم يلتزموا ذلك ، #بل_استحلوا أن يحكموا بخلاف ما أنزل الله فهم كفار ، #وإلا كانوا جهالا ، #كمن_تقدم_أمرهم ]

[ ብዙ ሠዎች ወደ ኢስላም ገብተዋል፡፡ ከዚህም ጋር ግን ያቺ አለቆቻቸው የሚያዙበት የሆነው ልማዳው በሆነው ነገር ላይ እንጂ አይፈርዱም፡፡ እነዚህ ሠዎች አሏህ ባወረደው ነገር እንጂ መፍረድ እንደሚይቻል ካወቁ ፣ ያንንም ተግባራዊ ካላደረጉ እንደውም አሏህ ካወረደው ( ህግ ) ውጪ መፍረድ #ሃላል_ካደረጉ እነሱ ካፊሮች ናቸው፡፡ ይህ ካልሆነ ግን ጃሂሎች ናቸው፡፡ የነሱ ጉዳይ እንዳሳለፍናቸው ሠዎች ጉዳይ ነው፡፡ ]

📚ሚንሃጁ ሡናህ: 130

፨ በነዚህ የኢብኑ ተይሚያህ ንግግሮች ላይ አሏህ ባወረደው ሁክም መፍረድ መተው ብቻ ኩፍር አክበር ነው የሚል መልዕክት አለን? ...  እስቲ ንግግሮቹ አንድ በአንድ እንያቸው፡፡

1ኛ). መጀመርያ ላይ ካፊር ይሆናሉ ያላቸው ሠዎች አሏህ ባወረደው ነገር ላይ መፍርድ ግዴታ አይደለም ብለው #የሚያምኑ ናቸው፡፡
2ኛ). ካፊር ያላቸው ሠዎች በሠዎች መካከል ከአሏህ ሌላ በሆነ አመለካከት መፍረድ ሃላል ነው የሚሉ ሠዎች ነው፡፡
3ኛ). ሠዎች ወደኢሥላም ከገቡ በኋላ አሏህ ካወረደው ህግ ውጪ በድሮ ልማዳቸው ይፈርዳሉ አለ፡፡ ታዲያ ኢብኑ ተይሚያህ ከአሏህ ውጪ ባለ ነገር መፍረድ መተዋቸው ብቻ ካፊር ያደርጋቸዋል አለን? በፍፁም...ይኸው ንግግሩ
ويرون أن هذا هو الذي ينبغي الحكم به دون الكتاب والسنة وهذا هو الكفر
" ይህ የነሱ (ልማዳዊ ህጋቸው) ከኪታብና ሡና ውጪ ሊፈርዱበት የሚገባ መሆኑ ያምናሉ፡፡ "

እዚህ ቦታ እነዚህ ሠዎች ኩፍር ላይ የጣላቸው በአሏህ ሁክም አለመፍረዳቸው ብቻ ሳይሆን ካለመፍረዳቸው ጋር በዘልማድ የያዙትን ህግጋት ከአሏህ ኪታብና ከረሡል ሡና ውጪ ሊፈርዱበት የሚገባ አድርገው ያምኑበት ነበር፡፡ በአጭሩ የነሱን ሁክም ከአሏህ ሁክም የተሻለ እንደሆነ ያምኑ ነበር፡፡ ይህ ነው ይህ ነው ኩፍር የሚሆነው፡፡ (هو الذي ينبغي الحكم به دون الكتاب والسنة) ማለታቸው ነው ኩፍር ላይ የሚጥላቸው፡፡

*** ሁለተኛው የኢብኑ ተይሚያህ ንግግር ሥንመለከት ***

1ኛ). ብዙ ሠዎች ወደኢሥላም እንደገቡ ቢገልፅም እነዚህ ሠዎች በአሏህ ኪታብ አይፈርዱም ነበር፡፡ ነገርግን እነዚህ ሠዎች በአሏህ ኪታብ አለመፍረዳቸው ብቻ ካፊር አደረጋቸውን? በፍፁም ! ንግግሩን እንይ..

فهؤلاء إذا عرفوا أنه لا يجوز الحكم إلا بما أنزل الله فلم يلتزموا ذلك ، #بل_استحلوا أن يحكموا بخلاف ما أنزل الله فهم كفار
" እነዚህ (ሠዎች) አሏህ ባወረደው ሁክም እንጂ መፍረድ እንደማይቻል ካወቁ ግን ያንን ተግባር ባያውሉት እንደውም አሏህ ካወረደው ተፃራሪ በሆነ ነገር መፍረድን ሃላል ካደረጉ እነሱ ካፊሮች ናቸው፡፡ "

ኢብኑ ተይሚያህ እነዚህ ሠዎች የሚከፍሩት አሏህ ባወረደው ነገር አለመፍረዳቸው ብቻ ሳይሆን ከአሏህ ህግ ተቃራኒ በሆነ ነገር መፍርድ #ሐላል ነው በማለታቸው እንደሆነ ያስታውቃል፡፡

ስለዚህ አለመፍረድ ብቻው ያከፍራል የሚለው ባጢል ነው ማለት ነው፡፡ ካለመፍረዳቸው ጋር ኢስቲህላል ፣ ኢስቲክባር ፣ ተፍዲል ፣ ጁሁድ የመሣሠሉት ነገሮች ተከትለው ከሆነ ነው የሚከፍረው!

፨ አሁን ወደሌላው የኢብኑ ተይሚያህ ንግግር እንለፍ!

"وَقَالَ تَعَالَى: {فَلَا وَرَبِّكَ لَا يُؤْمِنُونَ حَتَّى يُحَكِّمُوكَ فِيمَا شَجَرَ بَيْنَهُمْ ثُمَّ لَا يَجِدُوا فِي أَنْفُسِهِمْ حَرَجًا مِمَّا قَضَيْتَ وَيُسَلِّمُوا تَسْلِيمًا} فَمَنْ لَمْ يَلْتَزِمْ تَحْكِيمَ اللَّهِ وَرَسُولِهِ فِيمَا شَجَرَ بَيْنَهُمْ فَقَدْ أَقْسَمَ اللَّهُ بِنَفْسِهِ أَنَّهُ لَا يُؤْمِنُ، وَأَمَّا مَنْ كَانَ مُلْتَزِمًا لِحُكْمِ اللَّهِ وَرَسُولِهِ بَاطِنًا وَظَاهِرًا، لَكِنْ عَصَى وَاتَّبَعَ هَوَاهُ، فَهَذَا بِمَنْزِلَةِ أَمْثَالِهِ مِنَ الْعُصَاةِ. وَهَذِهِ الْآيَةُ مِمَّا يَحْتَجُّ بِهَا الْخَوَارِجُ عَلَى تَكْفِيرِ وُلَاةِ الْأَمْرِ الَّذِينَ لَا يَحْكُمُونَ بِمَا أَنْزَلَ اللَّهُ،" {منهاج السنة (٥/١٣١)}

- አላህ እንዲህ ይላል [ በጌታህም እምላለሁ በመካከላቸው በተከራከሩበት ፍርድ እስከሚያስፈርዱህ ከዚያም ከፈረድከው ነገር በነፍሶቻቸው ውስጥ ጭንቀትን እስከማያገኙና ፍፁም መታዘዝንም እስከሚታዘዙ ድረስ አያምኑም ]

" በመካከላቸው በተፈጠረ ነገር የአሏህ ና የመልዕክተኛውን ፍርድ በተግባር ያላስገኘ ሠው አሏህ በራሱ እየማለ ያ ሠው አያምን ብሏል፡፡ ነገር ግን የአሏህና የመልዕክተኛው ሁክም በውጩም በውስጡም ተግባራዊ ያደረገ ሠው ነገርግን አመፀ ሥሜቱም ተከተለ ይህ እንደአምሳዮቹ የወንጀል ባለቤት ነው፡፡ ይህ አንቀፅ ኸዋሪጆች እነዚያ  አሏህ ባወረደው ነገር የማይፈርዱ መሪዎች ለማክፈር ማሥረጃ አድርገው ተጠቅመውታል፡፡ "

📚 ሚንሃጅ አሥ-ሡናህ 5/131

፨ ከዚህ የሼይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ ንግግር የምናገኛቸው ቁምነገሮች ...

1ኛ). በመካከላችን በሚፈጠር ነገር በአሏህና መልዕክተኛው ፍርድ መፍረድ እንዳለብን!
2ኛ). በመካከላቸው በተፈጠረው ነገር በአሏህና በመልዕክተኛው ፍርድ የማይፈርዱ አሏህ እየማለ አያምኑም ብሏል፡፡
3ተኛ). የአሏህና የመልዕክተኛ ሁክምን በውጭም በውስጥ አረጋግጦ ነገርግን ስሜቱን በመከተል ካመፀ ከወንጀለኛ መሆኑ፡፡
4). ኸዋሪጆች አሏህ ባወረደው ነገር የሚፈርዱ መሪዎች በዚህ አንቀፅ ተጠቅመው እንደሚያከፍሩ አይተናል፡፡

፨ ኢብኑ ተይሚያህ በአሏህ ና መልዕክተኛ ፍርድ የማይፈርዱ ሲል ሁሉንም እንዳላካተተ በዚሁ ፅሁፍ መረዳት ይቻላል፡፡ ወይም ደግሞ በአሏህ ኪታብ መፍረድ መተው ብቻ ኩፍር አክበር ቢሆን ኖሮ እነዛ ወንጀለኞቹም ካፊር በተባሉ ፣ ኸዋሪጆቹም ባልተወቀሱ ነበር፡፡

ምክንያቱም ስሜቱ ተከትሎ በአሏህ ሸሪዐ ያልፈረደውና እነዚያ ኸዋሪጆች ያከፈሯቸው መሪዎች ሁሉ [ አሏህ ባወረደው ሸሪዐ የማይፈርዱ] (ومن لم يحكم بما أنزل الله) ናቸው፡፡ ለዚህ ነው ሡረቱል ማኢዳ ዟሂሩ ኩፍር አክበር አይጠቁምም የሚባለው፡፡ አይ ዟሒሩ ኩፍር አክበር የሚል ሠው እንደገና መጥቶ በስሜቱ የፈረደ ፣ በሸሪዐ ያልፈረደ መሪ ፣ በአንድ ሁለት ነጥብ የፈረደ ሠው አይከፍርም ሲል ከሠማኸው የአንቀፁ ዟሒር ዑሙም እንደሆነ ያልተረዳ መሃይም እንደሆነ እወቅ፡፡

፨ ኢብኑ ተይሚያህ ከላይ በተለያየ ንግግሮች ተፍዲል ፣ ወይም ኢስቲህላል ሸርጥ ማድረጉ አሳልፈናል፡፡

፨ ሌላው አል-ሁክም ቢገይሪ ማ አን-ዘለሏህ (الحكم بغير ما أنزل الله) ሼይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ ኩፍር ከማይሆኑ ወንጀሎች መድቦታል፡፡ ይኸው ንግግሩ ....

وَأَمَّا الْمَعَاصِي الَّتِي لَيْسَ فِيهَا حَدٌّ مُقَدَّرٌ وَلَا كَفَّارَةٌ كَاَلَّذِي يُقَبِّلُ الصَّبِيَّ وَالْمَرْأَةَ الْأَجْنَبِيَّةَ أَوْ يُبَاشِرُ بِلَا جِمَاعٍ أَوْ يَأْكُلُ مَا لَا يَحِلُّ كَالدَّمِ وَالْمَيْتَةِ أَوْ يَقْذِفُ النَّاسَ بِغَيْرِ الزِّنَا أَوْ يَسْرِقُ مِنْ غَيْرِ حِرْزٍ وَلَوْ شَيْئًا يَسِيرًا أَوْ يَخُونُ أَمَانَتَهُ كَوُلَاةِ أَمْوَالِ بَيْتِ الْمَالِ أَوْ الْوُقُوفِ وَمَالِ الْيَتِيمِ وَنَحْوِ ذَلِكَ إذَا خَانُوا فِيهَا وَكَالْوُكَلَاءِ وَالشُّرَكَاءِ إذَا خَانُوا أَوْ يَغُشُّ فِي مُعَامَلَتِهِ كَاَلَّذِينَ يَغُشُّونَ فِي الْأَطْعِمَةِ وَالثِّيَابِ وَنَحْوِ ذَلِكَ أَوْ يُطَفِّفُ الْمِكْيَالَ وَالْمِيزَانَ أَوْ يَشْهَدُ بِالزُّورِ أَوْ يُلَقِّنُ شَهَادَةَ الزُّورِ أَوْ #يَرْتَشِي_فِي_حُكْمِهِ أَوْ #يَحْكُمُ_بِغَيْرِ_مَا_أَنْزَلَ_اللَّهُ أَوْ يَعْتَدِي عَلَى رَعِيَّتِهِ أَوْ يَتَعَزَّى بِعَزَاءِ الْجَاهِلِيَّةِ أَوْ يُلَبِّي دَاعِيَ الْجَاهِلِيَّةِ إلَى غَيْرِ ذَلِكَ مِنْ أَنْوَاعِ الْمُحَرَّمَاتِ : فَهَؤُلَاءِ يُعَاقَبُونَ تَعْزِيرًا وَتَنْكِيلًا وَتَأْدِيبًا بِقَدْرِ مَا يَرَاهُ الْوَالِي #عَلَى_حَسَبِ_كَثْرَةِ_ذَلِكَ الذَّنْبِ فِي النَّاسِ وَقِلَّتِهِ . #فَإِذَا_كَانَ_كَثِيرًا زَادَ فِي الْعُقُوبَةِ #بِخِلَافِ_مَا_إذَا_كَانَ_قَلِيلًا .)

[ የተወሰነ የሆነ ገደብና ከፋራህ የሌላቸው ወንጀሎች የሚባሉት ህፃንና ባዕድ ሴትን የሚሥም ወይም ያለ ግኑኝነት የሚደባብስ ፣ ወይም ሃላል ያልሆነ ነገር የሚበላ ደም በክት ይመሥል.....] ቀጠለና ለማሳጠር [ በውሸት የሚመሠክር ፣ወይም የውሸት ምሥክርነትን የሚያቀብል ወይም በሁክሙ ላይ ጉቦ የሚቀበል ፣ ወይም ደግሞ #አሏህ_ባላወረድ_ነገር_የሚፈርድ ወይም ከሥሩ ባሉ ሠዎች ድንበር የሚያልፍ...]

፨ በማለት ይዘረዝራል፡፡ እነዚህ የዘረዘራቸው ሁሉ አሏህ ባላወረደው ነገር መፍረድ ጀምሮ ከማያከፍሩ ወንጀሎች የሚመደቡ ናቸው፡፡

፨ ሌላው አንድ ጊዜ ከፈረደ ፣ ሁለት ጊዜ ከፈረደ የሚባለው ፍልስፍና ኢብኑ ተይሚያህ ውድቅ ሲያደርገው እንዲህ ብሏል ፦

فَهَؤُلَاءِ يُعَاقَبُونَ تَعْزِيرًا وَتَنْكِيلًا وَتَأْدِيبًا بِقَدْرِ مَا يَرَاهُ الْوَالِي #عَلَى_حَسَبِ_كَثْرَةِ_ذَلِكَ الذَّنْبِ فِي النَّاسِ وَقِلَّتِهِ . #فَإِذَا_كَانَ_كَثِيرًا زَادَ فِي الْعُقُوبَةِ #بِخِلَافِ_مَا_إذَا_كَانَ_قَلِيلًا

[ እነዚህ ሠዎች {ከላይ የዘረዘራቸው አሏህ ባላወረደው የሚፈርደው ጨምሮ ማለት ነው፡፡ } እነዚህ ሠዎች ለማሥጠንቀቅና ዐደብ ለማሥያዝ ለመቅጣትም ባለሥልጣኑ ይሆናል ባለው ልክ ይቀጣሉ፡፡ ያንን ወንጀል በሠዎች ያለው ብዛትነት እና ትንሽነት ታይቶ ነው፡፡ (ወንጀሉ) ብዙ ከሆነ ትንሽ ከሆነው በተቃራኒ  ቅጣቱም ይጨምራል፡፡ ]

፨ ይህ ማሥረጃ ሼይኹል ኢስላም ላይ እንጠለጠላለሁ ለሚል ሠው ሁሉ በአፍ ጢሙ የምትደው ነች፡፡ አሏህ ባወረደው የማይፈርድ ሁሉ #ካፊር ነው የሚሉ ሠዎች ከኢብኑ ተይሚያ መንሐጅ የጠሩ መሆናቸው ታውቃለህ፡፡

ሌላው በአሏህ ባላወረደው ነገር መፍረዱ የፈለገ ያህል ቢጨምር ፣ ቅጣቱ ይጨምራል እንጂ ከኢስላም አያስወጣውም፡፡ ምክንያቱም እንደማንኛውም ወንጀል ነው፡፡

አሏህ ባላወረደው መፍረድ በልቁ ኩፍር አክበር ቢሆን ኖሮ አንድም ጊዜ ፈረደ ፤ ሁለት ጊዜም ፈረደ ኩፍር ይሆን ነበር፡፡ ግን ጂንሡ ወይም መሠረቱ ከወንጀሎች የሚመደብ ሥለሆነ ኩፍር ለመሆኑ የግድ ቀራኢን (ተያያዥ) ነገሮች መኖር አለባቸው፡፡ ኢስቲህላል (በሌላ መፍረድ ሃላል ነው ማለት) ፣ ወይም ጁሁድ (የአሏህ ሁክም መሆኑ በማሥተባበል) ፣ ኢስቲክባር (እንደ ኢብሊስ) ፣ ተፍዲል ( የሌላን ሁክም ከአሏህ ሁክም ይበልጣል ማለት ) የመሳሰሉ ቀሪናዎች ሊኖሩ ግድ ነው፡፡

፨ ታዲያ አሁን አንድ ሠው መጥቶ በየትኛው ድፍረቱ ነው ኢብኑ ተይሚያ በአሏህ ሁክም መፍረድ መተው ብቻው ያከፍራል የሚለው?

፨ አሏህ ወደ ሐቅ ይምራን፡፡ ወልሃምዱሊላሂ ረቢል ዐለሚን፡፡


Wednesday, September 16, 2020

፨ የኢማም ኢብኑል ቀይም (ረሂመሁሏህ) ንግግርና የአቡ ጧኢሽ ጅሕልና !!

፨ የኢማም ኢብኑል ቀይም (ረሂመሁሏህ) ንግግርና የአቡ ጧኢሽ ጅሕልና !!

❀❀❀❀  በአሏህ ሥም እጅግ በጣም ሩህሩህና እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው እጀምራለሁ፡፡ ❀❀❀❀

በዚህ ፅሁፍ በአሏህ ፍቃድ የኸዋሪጆችን ሹብሃ ያደናገራቸው ሠዎች ከሚያነሷቸው ነጥቦች ፣ ሹብሃ እንኳን የማይባሉ ነገሮች አንዱ የኢማም ኢብኑል ቀይም (ረሂመሁሏህ) ንግግር ነው፡፡

እስቲ የአቡ ጧኢሽ ምልከታዎች በከፊሉ እየተመለከትን ያለ ዕውቀቱ የዘባረቀውን እናጥራ፡፡

[  በምናደርገው ውይይት ከሱ የዐረብኛ እውቀት አናሳ መሆን የተነሳ የሸይኽ ሱለይማንን ንግግር ቆርጬ በማምጣት ወቅሶኝ ካበቃ በኋላ ቻናሉ ላይ በሚያሳፍር ሁኔታ የኢብን አል ቀይምን ንግግር ቆራርጦ አመጣና ኢብን አል ቀይም እንደራሱ የተጣመመ አመለካከት ያላቸው በማስመስል ሰውን
ሊያጭበረብርበት ሞከረ። ] ይላል አቡ ኢምራን (አቡ ጧኢሽ)፡፡

መልስ ፦ እዚህ ቦታ ሁለት ነገሮች አነሳለሁ፡፡ አንደኛው እኔን በዐረብኛ እውቀት ማነስ መኮነኑ ሲሆን በእርግጥም እኔ በዐረብኛ የመጠቀ እውቀት የለኝም፡፡ ነገርግን ኑሱሶች የምረዳበት ያህል ግን አውቃለሁ፡፡ አልሃምዱሊላህ፡፡ ወደፊትም በደንብ እማራለሁ፡፡ ነገር ግን አቡ ኢምራን አንድ የአረብኛ ቋንቋ ገና ጀማሪ የሆነ ተማሪ ሠው እንኳን የማይሳታቸው ስህተቶች በርካታ ቦታ ይሳሳታል፡፡ ለምሳሌ የሠዎች ሥም ሲፅፍ እንዲህ ነው፡፡
عبد الله ابن صالح ابن محمد ابن محمد
• እንግዲህ አጁሩሚያህ የሞጠለ ሠው በዚህ ሁኔታ ፅሁፍ ይፅፋል ብዬ አልጠብቅም፡፡ በሁለት ዐለመይን መካከል አሊፍ ስትወድቅ አትፃፍም፡፡ የምትጻፈው የመጀመርያ ሠጥር ላይ ካገኘናት ነው፡፡ እነዚህ ነገሮች ማሥተካከል የማያውቅ ሙቀት የሞላው ጃሂል እከሌ ዐረብኛ አያውቅም ሲል ያሳፍራል፡፡ እኔ በራሴ በዐረብኛ ብዙ እውቀት የለኝም፡፡ እንዲህ የወረደ ነገር ግን ኢንሻ አሏህ አልሳሳትም፡፡ ደሞ አንዴ ቢሆን ተሳስቶ ነው ትላለህ ሲደጋገምስ?
عبد الله بن صالح بن محمد بن محمد....
እያልክ መፃፍ ይኖርብሃል፡፡ እኛ ዐረብኛ ከሚያስተምሩን ሼይኾች የተማርነው ይህ ነው፡፡

• ሁለተኛው ፦ የኢብኑል ቀይም ንግግር አሳስቶ የተረጎመበት ሲሆን ይህ ወደኋላ እንመለከተዋለን፡፡

- በመቀጠል የኢማም ኢብኑል ቀይም ረሂመሁሏህ ንግግር አመጣውና እንዲህ አለ [ አቡ ሙስሊም ይህን የኢብን አል ቀይም ንግግር አልተረጎመውም እንዳለ ነው
ቁጭ ያደረገው ምክንያቱም ከተረጎመው አቂዳዬ ብሎት የያዘውን ያፈርስበታልና ነው፡፡ ] ይላል፡፡

መልስ ፦ እኔ የኢብኑል ቀይም ንግግር ያልተረጎምኩት ዐቂዳዬ ስለሚፃረር አይደለም፡፡ ዐቂዳዬ የሚፃረር ነገር በዐረብኛ ስላስቀመጥኩት ምን ይጠቅመኛል? እኔ ዐረብኛ አላውቅም ቢባል እንኳን በቻናሌ ዐረብኛ የሚያውቁ አሉ! የዚህ ልጅ ንግግሮች እኮ መልስ ሊሰጣቸው ቀርቶ መሳሳቂያ ናቸው፡፡ እስቲ የኢብኑል ቀይም ንግግር የማን ዐቂዳ እንደሚያወድም እናያለን፡፡

[ ለማንኛውም ዋናው የአቡ ሙስሊም ቅጥፈት ኢብን አል ቀይም ይህን ንግግር ከማስቀመጣቸው በፊት የተናገሩትን ነገር መተው ነው። ይህን ንግግር ከመናገራቸው በፊት ሸይኹ ያስቀመጡት ገለፃ አቡ ሙስሊም ወደ ግሩፕ ሊወያየኝ የመጣበትን አመለካከት እንዳለ ውድቅ የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ በሰው ላይ የሚቀጥፍ መሆኑንም የሚያጋልጥ ነው። ] ይላል፡፡

መልስ ፦ እኔ ያቀረብኩት ንግግር ኢብኑል ቀይም ረሂመሁሏህ የተለያዩ አመለካከቶች ያቀራባቸውን ንግግሮች ከጨረሰ በኋላ እሱ ዘንድ ትክክለኛውን አቋም ብሎ የተናገረውን ነው፡፡ ሌሎቹ ንግግሮች የኢብኑል ቀይም አቋም የሚገልፁ ሥላልሆኑ [ የኢብኑል ቀይም አቋም ይህ ነው] ብዬ ላቀርብ አልችልም፡፡ ነገርግን አጠቃላይ በቦታው የሠፈረው ነገር እያወራሁ ቢሆን ኖሮ የሌሎቹ ንግግር ለምን ተውከው ያስብላል፡፡ እኔ ግን ያደረግኩት የራሱ የኢብኑል ቀይም አቋም ነው ያመጣሁት ሥለዚህ ትክክል ነኝ ምንም ቅጥፈት የለውም፡፡

• ሌላው ኢብኑል ቀይም ረሂመሁሏህ ከንግግራቸው ቀድሞ ያመጧቸው ሃሳቦች የኔን አመለካከት ውድቅ የሚያደርጉ መሆናቸው ይናገራል፡፡ እዛ ጋ ያሉ ንግግሮች እኮ ትክክል አይደሉም ብለው የተናገሩት ራሳቸው ኢብኑል ቀይም ናቸው፡፡ አንባቢ ግራ እንዳይጋባ ሁሉም ንግግራቸው እንደሚከተለው አቀርበዋለሁ፡፡
.................................................................

📚 [ መዳሪጁ ሣሊኪን ] 1/ ገፅ 516-520 የኢማም ኢብኑል ቀይም ንግግር ከገጽ:516 ይጀምራል፡፡ የኢማም ኢብኑል ቀይም ንግግር በዚህ ምልክት 👉【】 ውስጥ ብቻ አስቀምጣለሁ፡፡ ሌላው የኔ ማብራርያ ነው፡፡
ኢብኑል ቀይም (ረሂመሁሏህ) የተለያዩ ወንጀሎችን ጠቅሰው እነዚህ ተውበት ሊደረግባቸው የሚገቡ ነጥቦች ናቸው በማለት የተለያዩ ወንጀሎችን ዘረዘሩ፡፡ እንዲህም አሉ ፦
【فأما الكفر، فنوعان : كفر أكبر وكفر أصغر 】

【ኩፍር (ክህደት) ሁለት አይነት ነው፡፡ ትልቁ ከህደት (ኩፍር አክበር) እና ትንሹ ክህደት (ኩፍር አስገር) ናቸው፡፡ 】

እንግዲህ አሁን ኢብኑል ቀይም የኩፍር አይነቶች ሊነገርን ነው፡፡ ከዚያ መካከል በቁርኣን "አሏህ ባወረደው ነገር የማይፈርዱ" (من لم يحكم بما أنزل الله) የሚለው ነጥብ ከኩፍር አክበር ይመድበዋል ወይስ ከኩፍር አስገር ይመድበዋል? የሚለው ወሳኝ ጥያቄ ነው፡፡ እንቀጥል...
【فالكفر الأكبر:  هو الموجب للخلود في النار.
والأصغر:  لاستحقاق الوعيد دون الخلود ،كما في قوله تعالى وكان مما يتلى فنسخ لفظه « لا ترغبوا عن آبائكم فإنه كفر بكم» وقوله في الحديث صحيح «اثنتان في أمتي، هما بهم الكفر ، الطعن في النسب والنياحة»】
【ትልቁ ኩፍር የሚባለው ፦ በእሳት ውስጥ መዘውተርን ግድ የሚያደርግ ኩፍር ነው፡፡ ትንሹ ኩፍር ደግሞ በእሳት ከመዘውተር ውጪ (ባነሰ) ለዛቻ የሚዳርግ ነው፡፡ አሏህ በንግግሩ እንዳለው ይህ ንግግሩ የሚነበብ ነበር ከዚያ ቃላቶቹ ተሽረዋል፡፡ "ከአባቶቻቹህ አትሽሹ ይህ በናንተ ላይ ኩፍር ነው፡፡" ሶሂህ በሆነ ሃዲስ ደግሞ " ሁለት ነገሮች በህዝቦቼ ውስጥ በነሱ ላይ ኩፍር ናቸው፡፡ በዘር ማነወርና በሟች ላይ እያለቀሱ መግጠም (ሙሾ)፡፡ 】

፨ ከዚህ የኢብኑል ቀይም ንግግር የምንረዳው ኩፍር ሁለት አይነት ነው፡፡ ትልቁና ትንሹ፡፡ አሁን ትንሹ ኩፍር የሆኑ ነገሮች እየዘረዘሩ ነው፡፡ በሸሪዐችን በዟሂር "ኩፍር" በሚል ቃል ተጠርተው ግን ትንሹ ኩፍር የሆኑ ነገሮች እየዘረዘሩ ነው፡፡ ትንሹ ኩፍር የተባሉ ነገሮች ጠቅሰው ከጨረሱ በኋላ ትልቁ የተባሉ ነገሮች ያመጣሉ፡፡ እንቀጥል...

【وقوله في سنن: « من أتى امرأة في دبرها فقد كفر بما أنزل على محمد صلى الله عليه وسلم»  وفي الحديث الآخر:  «من أتى كاهنا،  فصدقه بما يقول،  فقد كفر بما أنزل على محمد صلى الله عليه وسلم»، وقوله:  «لا ترجعوا  بعدي كفارا يضرب بعضكم رقاب بعض】

【የረሡል ﷺ ንግግር  በሡነኖች ውስጥ የተዘገበ እንዲህ ይላል ፦ "ሴት ልጅን ከኋላዋ በኩል የተገናኛት በሙሃመድ ﷺ ላይ በወረደው ክዷል፡፡ በሌላ ሃዲስ ደግሞ " ጠንቋይ ዘንድ የመጣ በሚናገረውም ነገር እውት ነው ያለ በርግጥም በሙሃመድ ﷺ  ላይ በወረደው ክዷል፡፡" ሌላም የረሡል ንግግር " ከኔ በኋላ  ከፊላቹህ የሌላውን አንገት የሚመታ ካፊር ወደ-መሆን አትመለሱ 】📚 [ መዳሪጁ ሣሊኪን ] 1/ ገፅ 518

፨ እንግዲህ ኢማም ኢብኑል ቀይም (ረሂመሁሏህ) ሸሪዐህ ኩፍር በማለት ቢገልፃቸውም ሐቂቃቸው ግን ትንሹ ኩፍር የሆኑ ነገሮች እየገለፁ ነው፡፡ አሁን ደግሞ እሳቸው እዚሁ ቦታ " አሏህ ባወረደው ነገር የማይፈርዱ" (من لم يحكم بما أنزل الله) የሚለው አንቀፅ ከትንሹ ኩፍር ዝርዝር ውስጥ በማሥቀመጥ እንዲህ ብለዋል...

【وهذا تأويل ابن عباس وعامة أصحابه في قوله تعالى "  ومن لم يحكم بما أنزل الله فأولئك هم الكافرون" قال ابن عباس:  ليس بكفر ينقل عن الملة،  بل إذا فعله فهو به كفر وليس كمن كفر بالله واليوم الآخر. وكذلك قال طاووس. وقال عطاء:  هو كفر دون كفر،  وظلم دون ظلم   وفسق دون فسق】

【ይህ (ኩፍር አስገር) የሚለው [ አሏህ ባወረደው ነገር የማይፈርዱ እነዚያ ካፊሮች እነሱ ናቸው፡፡] በሚለው የቁርኣን አንቀፅ ላይ የኢብኑ ዐባስ እና #የአጠቃላይ_ባልደረቦቹ ተፍሲር ነው፡፡ ኢብኑ ዐባስ እንዲህ አለ "ከኢሥላም የሚያስወጣ ኩፍር አይደለም፡፡ እንደውም ይህ ሥራ የሠራ ጊዜ በሡ ላይ ኩፍር ይሆንበታል፡፡ ይህ በአሏህና በመጨረሻው እንደመካድ አይደለም፡፡ ልክ እንደዚሁ ጣውውስ ብሏል፡፡ ዓጧእ ቢን ረባህ እንዲህ ብሏል "ኩፍሩን ዱነ ኩፍር ፣ ዙልሙን ዱነ ዙልም ፣ ፊስቁን ዱነ ፊስቅ】

፨ አሁን አቡ ኢምራን (አቡ ጧኢሽ) በጅህልናው ለሚዘባርቃቸው ነገሮች ኢብኑል ቀይም መልስ እየሠጡ ነው፡፡ ምን ለምሣሌ ብትሉኝ...

1ኛ). አቡ ጧኢሽ በተለያዩ ዝባዝንኬ ፅሁፎቹ የኢብኑ ዐባስ ተፍሢር ኩፍር አክበር ያመለክታል ሲል ሲፅፍ ነበር፡፡ ይኸው ኢብኑል ቀይም ኢብኑ ዐባስም ሆነ አጠቃላይ የኢብኑ ዐባስ ባልደረቦቹ ይህች አንቀፅ *ኩፍር አስገር* ታመለክታለች ብለው ያምኑ እንደነበር ይገልፃል፡፡ ሥለዚህ የዚህ ጧኢሽና የኢማሙ መንሐጅ ለየቅል ነው፡፡

2ኛ). የኢብኑል ቀይም ንግግር የአቡ ሙሥሊሥ አካሄድ ውድቅ ያደርጋል ሲል ነበር በተቃራኒው ኢብኑል ቀይም ይህን አንቀጽ ከኩፍር አስገር ዝርዝር ውስጥ አስቀምጠውታል፡፡ እሳቸውም የበለጠ ይጠቅሱታል፡፡ እንመጣበታለን፡፡

• እስቲ አሁን ኢማም ኢብኑል ቀይም ኺላፍ ብሎ ያመጣቸው ነገሮች እንያቸው ከዚያም የአቡ ጧኢሽ ፍልስፍና እናያለን፡፡ በዚህ ምልክት【  】የኢማም ኢብኑል ቀይም  ነቅል ነው የማስቀምጠው ...እንቀጥል፡፡
【ومنهم من تأول الآية على ترك الحكم بما أنزل الله جاحدا له ، وهو قول عكرمة وهو تأويل مرجوح، فإن نفس جحوده كفر سواء حكم أو لم يحكم】

【ከነሡ መካከል አንቀፁን አሏህ ባወረደው ነገር ሁክሙን  በማሥተባበል መፍረድ የተወን ሠው ያመልክታል ብለው የፈሠሩ አሉ፡፡ ይህ የዒክሪማህ ንግግር ነው፡፡ የሱ ተፍሲርም ሚዛን የማይደፋ ተፍሲር ነው፡፡ ማሥባበል ራሱ (አሏህ ባወረደው) ኩፍር ነው፡፡ ቢፈርድም ባይፈርድም እኩል ነው፡፡】

፨ ይህ የኢክራማህ ንግግር ሐቂቃው ለተረዳው ሠው የኢማም ኢብኑል ቀይም ንግግር አይጠፋውም፡፡ ይህ አንቀፅ በልቁ የተቀመጠና ዟሒሩ ሲታይ ዑሙም (ጥቅል መልዕክት) የሚሠጥ ነው፡፡ ስለዚህ ዟሒሩ በአንድ ጉዳይ ላይ የተገደበ አይደለም፡፡ ነገርግን ሠበቡ ኑዙሉ ላይ አይሁዶች የአሏህን ሁክም ጀህድ አላደረጉም ለማለት ነው ከተባለ ይህ ባጢል ነው ምክንያቱም በንግግሩ ላይ ስለዚያ ጉዳይ ጭራሽ አላነሳም፡፡ አይሁዶች ጀህድ አላደረጉም ሁክም የተወ ብቻ ይከፍራል ቢል ኖሮ ኢብኑል ቀይም የአቡ ጧኢሽ ዐቂዳ የሚያድመውን አቋማቸው ግልጽ ባላደረጉ ነበር፡፡ ሌላኛው ኺላፍ ያሉት ንግግር እንይ ...

【  ومنهم من تأولها على ترك الحكم بجميع ما أنزل الله: قال ويدخل في ذلك الحكم بالتوحيد والإسلام. وهذا تأويل عبد العزبز الكناني. وهو أيضا بعيد، إذ الوعيد على نفي الحكم بالمنزل ، وهو يتناول تعطيل الحكم بجميعه وببعضه】

【ከነሱም መካከል አጠቃላይ አሏህ ባወረደው ነገር መፍረድ የተወ ተፈልጎበት ነው ብሎ የፈሠረ አለ፡፡ እንዳለውም " በዚህ ውስጥ በተውሒድና በኢስላም መፍረድም ይካተታል" ብሏል፡፡ ይህ የዐብዱልዐዚዝ አል-ኪናኒ ተፍሢር ነው፡፡ ይህ ራሱ የራቀ ነው፡፡ በወረደው (ሸሪዐ) ሑክምን ውድቅ በማድረግ የመጣው ዛቻ ባጠቃላይ ሁክሞች ውድቅ ማድረግም ሆነ በከፊሎቹ አካቶ የሚይዝ ነው፡፡ 】

፨ ኢብኑል ቀይም ይህን ተፍሢር ውድቅ ያደረገበት ምክንያቱ አል-ኪናኒ እንዳለው አጠቃላይ ነገሮች ላይ መፍረድ ሲተው ነው የሚከፍረው የሚል አቋም ሲያንፀባርቅ ፣ ኢብኑል ቀይም ደግሞ አንቀጹ ላይ የተቀመጠው ዛቻ አጠቃላይ ነገሮች ላይ መፍረድ የተወ ብቻ ሳይሆን ከፊል ነገሮችም ላይ ሁክምን ውድቅ ያደረገ ያክታትል እያለ ነው፡፡ አሁንም ኢብኑል ቀይም የአንቀፁ ዑሙም መልዕክት አስረግጦ እየገለፀ ነው፡፡ ሌላኛው እንቀጥል...

【ومنهم من تأولها على الحكم بمخالفة النص تعمدا من غير جهل به ولا خطأ في تأويل، حكاه البغوي عن علماء عموما】

【ከነሱ መካከል  እያወቀ ጅህልና ሳይኖርበት በተዕዊል ላይ ሳይሳሳት የወህይ ማሥረጃዎችን በመቃረን ፍርድ መሥጠት ላይ የፈሠረው አለ፡፡ ከአጠቃላይ ዑለማዎች አልበገዊ አስተላልፎታል፡፡ 】

፨ ይህ የአል-በገዊ ተፍሢር ኢብኑል ቀይም እዚሁ ቦታ ውድቅ ሳያደርገው አልፎታል፡፡ ስለዚህ እንቀጥል ኺላፍ ብሎ ያመጣቸውን ...
【  ومنهم من تأولها على أهل الكتاب. وهو قول قتادة والضحاك وغيرهما. وهو بعيد خلاف ظاهر اللفظ فلا يصار عليه 】
【ከነሱ መካከል በመፅሃፍ ባለቤቶች ላይ የፈሠረው አለ፡፡ ይህ የቀታዳህ ፣ የአድዶሃክ የሌሎችም አቋም (ንግግር) ነው፡፡ ይህ ራሱ የራቀና በዟሒር ከሚታየው ቃል የሚፃረር ነው፡፡ ወደዚህ አቋም አይኬድም፡፡ 】

፨ በዚህ የኢብኑል ቀይም ረሂመሁሏህ ንግግር ቀታዳና ዶሃክ እንዲሁም ሌሎችም ንግግር የአንቀፁ ዟሂር አህሉል ኪታቦች የተገደበ እንዳልሆነ ያስቀምጣሉ፡፡ ይህ ሁሉም መረዳት ያለበት ነገር ነው፡፡ ሠበበ-ኑዙሉ አይሁዶች ላይ የወረደ መሆኑ ሁሉም ያውቃል፡፡ እዚህ ጋር ኢብኑል ቀይም የተቃወሙት የአንቀጹ ዟሒር ዑሙም ነው ነው፡፡ የተገደበ አይደለም፡፡ (خلاف ظاهر اللفظ) በማለት ኢብኑል ቀይም ያስቀምጣል፡፡ ይህ ሃቅ ነው ዟሒሩ አህሉል ኪታብ ላይ የተገደበ አይደለም፡፡ እንቀጥል ...
【  ومنهم من جعله كفرا ينقل عن الملة】
【 ከነሱ መካከል ከኢሥላም የሚስወጣ ኩፍር ያደረገው አለ፡፡ ]

፨ እዚህ ቦታ ኢብኑል ቀይም ይህ ንግግር ማን እንደተናገረ አላስቀመጠም፡፡ እንደዚህ የሚሉ እንዳሉ ግን በልቁ ነገረን፡፡ ነገርግን የኢብኑል ቀይም አቋም ይህ እንዳልሆነ በመቀጠል ራሱ ኢብኑል ቀይም ወስ-ሶሂሁ (وصحيح) ትክክለኛ አቋም በማለት አስቀምጧል እናየዋለን፡፡  ትክክለኛው አቋም ብሎ ማሥቀመጡ ከላይ ያሉ የሃሳብ ልዩነቶች ኢብኑል ቀይም እንዳልተቀበላቸው ማሳያ ነው፡፡

የደውላው አቡ ጧኢሽ እንዲህ ብሎ ነበር ፦ [ እኔ ይህች አያ ኩፍር አክበር ነች በማለቴ በተደጋጋሚ ይህ የኸዋሪጅ እንጂ
በጭራሽ የአህሉ ሱና አቋም አይደለም ሲለኝ ነበር] ብሏል፡፡

መልስ፦ ይህ አንቀፅ እንደአገባቡ ነው የሚፈሠረው ሁሌም የምለው ይህ ነው፡፡ ዟሒሩ ጥቅል መልዕክት ሥላለው ኩፍር አስገር የሚጠቁም ሲሆን ፣ አንቀፁ እንደወረደበት ሠበብ ከታየ ግን የአሏህን ሑክም ጀህድ ስላደረጉ አይሁዶች ነውና ኩፍር አክበር ነው፡፡ ይህ ነው ንግግሬ፡፡ አንተ እኮ የአንቀፁ ዟሂር ኩፍር አክበር ነው ትላለህ ይህ የኸዋሪጆች ዐቂዳህ እንደሆነ እኔ ሳይሆን ያስቀመጥኩት የአህሉ ሡና ዑለሞች ናቸው፡፡ ይኸው ንግግራቸው ላቅርብ..
❀ አቡል ሙዞፈር አሥ-ሠምዐኒ ረሂመሁሏህ በተፍሢሩ እንዲህ አለ ፦

ﻗﺎﻝ ﺃﺑﻮ ﺍﻟﻤﻈﻔﺮ ﺍﻟﺴﻤﻌﺎﻧﻲ ﻓﻲ ﺗﻔﺴﻴﺮﻩ ‏[ /2 42 ‏] : ﺍﻋﻠﻢ ﺃﻥ ﺍﻟﺨﻮﺍﺭﺝ ﻳﺴﺘﺪﻟﻮﻥ ﺑﻬﺬﻩ ﺍﻵﻳﺔ ﻭﻳﻘﻮﻟﻮﻥ ﻣﻦ ﻟﻢ ﻳﺤﻜﻢ ﺑﻤﺎ ﺃﻧﺰﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﻓﻬﻮ ﻛﺎﻓﺮ ﻭﺃﻫﻞ السنة ﻻ ﻳﻜﻔﺮﻭﻥ ﺑﺘﺮﻙ ﺍﻟﺤﻜﻢ. ﺍﻫـ
【እወቅ! ኸዋሪጆች በዚህ አንቀፅ ላይ ማሥረጃነት ይጠቀማሉ፡፡ አሏህ ባወረደው ነገር ያልፈረደ ካፊር ነው ይላሉ፡፡ #አህሉ_ሡናዎች ግን ሁክምን በመተው ብቻ #አያከፍሩም፡፡】

፨ ይህ የአህሉ-ሡና ዑለሞች ኢጅማዕ ነው፡፡ አቡ ጧኢሽና ጓደኞቹ ከዚህ በተቃራኒ ሁክም መተው ብቻ ያከፍራል ይላሉ፡፡ ታዲያ እኔ ነኝ እንዴ ኸዋሪጅ ያልኩህ ራስህ ኸዋሪጅ ሆነህ መጣህብን እንጂ... ሌላም ተመልከቱ

ኢብኑ ዐብዱልበር [ አት-ተምሂድ 16/17]

ﻗﺎﻝ ﺍﺑﻦ ﻋﺒﺪ ﺍﻟﺒﺮ ﻓﻲ ﺍﻟﺘﻤﻬﻴﺪ ‏[ 16 /17 ‏] : ﻭﻗﺪ ﺿﻠﺖ ﺟﻤﺎﻋﺔ ﻣﻦ ﺃﻫﻞ ﺍﻟﺒﺪﻉ ﻣﻦ ﺍﻟﺨﻮﺍﺭﺝ ﻭﺍﻟﻤﻌﺘﺰﻟﺔ ﻓﻲ ﻫﺬﺍ ﺍﻟﺒﺎﺏ ﻭﺍﺣﺘﺠﻮﺍ ﺑﺂﻳﺎﺕ ﻟﻴﺴﺖ ﻋﻠﻰ ﻇﺎﻫﺮﻫﺎ ﻣﺜﻞ ﻗﻮﻟﻪ ﻋﺰ ﻭﺟﻞ : } ﻭﻣﻦ ﻟﻢ ﻳﺤﻜﻢ
ﺑﻤﺎ ﺃﻧﺰﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﻓﺄﻭﻟﺌﻚ ﻫﻢ ﺍﻟﻜﺎﻓﺮﻭﻥ {. ﺍﻫـ
【በዚህ ርዕስ ላይ በርግጥም ከቢድዐ ባለቤት የሆኑ  ጀመዐዎች ጠመዋል ፤ ኸዋራጆችና ሙዕተዚላዎች፡፡ በዟሂር ትርጉሟ በማትያዝ አንቀፅ ላይ ማሥረጃን አደረጉ፡፡ ለምሳሌ "አሏህ ባወረደው ነገር የማይፈርዱ እነዚያ ከሃዲዎች እነሱ ናቸው፡፡ " የሚለው አንቀፅ፡፡】

፨ ይኸው በግልፅ ኸዋሪጆች አንቀፁ በዟሂሩ ይፈስሩት ነበር፡፡ አቡ ጧኢሽም እያደረገ ያለው ይኸው ነው፡፡ እስቲ በሱ መንሃጅ ላይ ነኝ የሚለው ኢብኑ ተይሚያህ የሚለው እንይ...

ﻭﻗﺎﻝ ﺷﻴﺦ ﺍﻹﺳﻼﻡ ﺍﺑﻦ ﺗﻴﻤﻴﺔ ﻓﻲ ﻣﻨﻬﺎﺝ ﺍﻟﺴﻨﺔ ‏[ 5 / 131 ‏] : } ﻓﻼ ﻭﺭﺑﻚ ﻻ ﻳﺆﻣﻨﻮﻥ ﺣﺘﻰ ﻳﺤﻜﻤﻮﻙ ﻓﻴﻤﺎ ﺷﺠﺮ ﺑﻴﻨﻬﻢ .... { ﻭﻫﺬﻩ ﺍﻵﻳﺔ ﻣﻤﺎ ﻳﺤﺘﺞ ﺑﻪ ﺍﻟﺨﻮﺍﺭﺝ ﻋﻠﻰ ﺗﻜﻔﻴﺮ ﺍﻟﻮﻻﺓ ﺍﻟﺬﻳﻦ ﻳﺤﻜﻤﻮﻥ ﺑﻐﻴﺮ ﻣﺎ ﺃﻧﺰﻝ ﺍﻟﻠﻪ. ﺍﻫـ
【በጌታህም እምላለሁ በመካከላቸው በተከራከሩበት ፍርድ እስከሚያስፈርዱህ...ድረስ አያምኑም" ይህ አንቀፅ ኸዋሪጆች አሏህ ባወረደው ነገር የማይፈርዱ መሪዎችን ለማክፈር ለማሥረጃነት ይጠቀሙበታል፡፡ 】

፨ ኢብኑ ተይሚያህ አሏህ ባወረደው ነገር የማይፈርዱ ሙስሊም መሪዎች እንዳሉ ጭምር እየጠቆመ ነው፡፡ አቡ ጧኢሽ ደግሞ የማይፈርዱ ሁሉ ካፊር ነው ይላል፡፡ ሥለዚህ ከኸዋሪጆች በምን ተለየህብን፡፡ ከነሱ የተለየ ያልከው ምን አለ? እስቲ የሚለው አንብቡ...

[ ከዚህ በታች ያለው ፅሁፍ ኢብን አል ቀይም የመረጡትን አቋም እና ኩፍር አስገር ነው ያሉት በአንድ ወይ ሁለት ጉዳይ ላይ ድንገት ድንበር ያለፈን ብቻ እንጂ በዘመናችን ያሉትን
የአሜሪካን እና እንግሊዝ ባሪያ የሆኑትን ጠዋጊቶች (የአቡ ሙስሊም ወዳጆች) እንደማይጨምር ያረጋገጥኩበት ነው። ] ይላል የደውላው ሼይኽ አቡ ጧኢሽ...

መልስ:- በዚህ የጅህልና ንግግሩ ጭራሽ በኢብኑል ቀይም ንግግር ላይ የሌሉ ጥመቶቹን አነባብሮ አስቀምጧል፡፡

1ኛው). [ ኩፍር አስገር ነው ያሉት በአንድ ወይ ሁለት ጉዳይ ላይ ድንገት ድንበር ያለፈን ብቻ እንጂ...] ብሏል፡፡ ይህን ቅጥፈት በሚከተለው የኢብኑል ቀይም ንግግር በማብራራት እንየው!

【ﻭﺍﻟﺼﺤﻴﺢ ﺃﻥ ﺍﻟﺤﻜﻢ ﺑﻐﻴﺮ ﻣﺎ ﺃﻧﺰﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﻳﺘﻨﺎﻭﻝ ﺍﻟﻜﻔﺮﻳﻦ ﺍﻷﺻﻐﺮ ﻭﺍﻷﻛﺒﺮ ﺑﺤﺴﺐ ﺣﺎﻝ ﺍﻟﺤﺎﻛﻢ، ﻓﺈﻧﻪ ﺇﻥ ﺍﻋﺘﻘﺪ ﻭﺟﻮﺏ ﺍﻟﺤﻜﻢ ﺑﻤﺎ ﺃﻧﺰﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﻓﻲ # ﻫﺬﻩ _ ﺍﻟﻮﺍﻗﻌﺔ ﻭﻋﺪﻝ ﻋﻨﻪ ﻋﺼﻴﺎﻧﺎً ﻣﻊ ﺍﻋﺘﺮﺍﻓﻪ ﺑﺄﻧﻪ ﻣﺴﺘﺤﻖ ﻟﻠﻌﻘﻮﺑﺔ ﻓﻬﺬﺍ ﻛﻔﺮ ﺃﺻﻐﺮ، ﻭﺇﻥ ﺍﻋﺘﻘﺪ ﺃﻧﻪ ﻏﻴﺮ ﻭﺍﺟﺐ ﻭﺃﻧﻪ ﻣﺨﻴﺮ ﻓﻴﻪ ﻣﻊ ﺗﻴﻘﻨﻪ ﺑﺄﻧﻪ ﺣﻜﻢ ﺍﻟﻠﻪ ﻓﻬﺬﺍ ﻛﻔﺮ ﺃﻛﺒﺮ، ﻭﺇﻥ ﺟﻬﻠﻪ ﻭﺃﺧﻄﺄﻩ ﻓﻬﺬﺍ ﻣﺨﻄﺊ ﻟﻪ ﺣﻜﻢ ﺍﻟﻤﺨﻄﺌﻴﻦ】

【ትክክለኛ (አቋም) አሏህ ባላወረደው ነገር መፍረድ እንደ ሃኪሙ (ፈራጁ) ሁኔታ ሁለቱንም የኩፍር አይነቶች ያካትታል፡፡ ትንሹም ትልቁም፡፡ ሠውዬው በዚህች ክስተት አሏህ ባወረደው ነገር መፍረድ ግዴታነቱ #የሚያምን ከሆነና ለቅጣት የሚዳርገው መሆኑን እያረጋገጠ ለማመፅ በሚል ቢያዘነብል ይህ ኩፍር አስገር ነው፡፡ ግዴታ አይደለም ብሎ ቢያምንና እኔ ምርጫ አለኝ ቢል የአሏህ ፍርድ መሆኑን እርግጠኛ ሆኖ ይህ ትልቁ ኩፍር ነው፡፡ ባያውቀውና ቢሳሳት ይህ ተሳሳች ነው፡፡ ስህተት ላይ የወደቁ ሠዎች ሑክም አለው፡፡ 】📚መዳሪጁ አሥ-ሣሊኪን

፨ በዚህ ንግግር ላይ ኢብኑል ቀይም አንድ ጊዜ ፣ ሁለት ጊዜ ፣ ሶስት ጊዜ የሚል ንግግር ጭራሽ የላቸውም፡፡ እንዲህ ለማለት የሚወስድ ፍንጭ እንኳን የለውም፡፡ በዚህች ክስተት () ያሉት እየተናገሩበት ያለውን የፍርድ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህ በዚህ ብለው አልገደቡትም፡፡ በቁጥርም አልገለፁትም፡፡ (الواقعة) የሚለው ቃል ጥቅል መልዕክት የሚያስተላልፍ ነው፡፡ አንድ ይሁን ሁለት ይሁን እየተናገሩ አይደለም፡፡ ለዚህም ነው ሼይኹ " ከሱ የተዘነበለ" (ﻭﻋﺪﻝ ﻋﻨﻪ) ማለት ከአሏህ ሑክም የተዘነበለ እያሉ ነው፡፡ አቡ ጧኢሽ በጅህልናው እንደዘባረቀው ሼይኹ (الواقعة) ክስተት እየተናገሩ ቢሆን ኖሮ (وعدل عنها) ይሉ ነበር፡፡ ምክንያቱም (الواقعة) የሚለው ተእኒስ እንስት መደብ ላይ የተቀመጠ ነው፡፡ ሼይኹ ያሉት ግን አጠቃላይ ንግግራቸው የሚያጠነጥንበት የአሏህ ሁክምን በተመለከተ ነው የተናገሩት፡፡ ስለዚህ "አል-ዋቂዐህ" የሚለው የቁጥር ብዛት የሚያመለክት አይደለም፡፡

፨ በመቀጠል ማንሳት ያለብኝ ነጥብ አንድ ሃኪም በአንድ መሥዐላ ቢፈርድ ፣ በሶስት መሥዐላ ሲፈርድ መዐሲ (ወንጀል) ነው ከተባለ ፣ በአንድ ሺህ ነገር ሲፈርድ ኩፍር የሚሆንበት በምን አግባብ ነው? ዐጂብ ይህ ሠው ቢያንስ ሁኔታው ወንጀል ላይ ዘውታሪ (ሙሲር አል-መዐሲ) ተብሎ ነው የሚገለፀው፡፡ እንጂ ካፊር አይባልም፡፡ የኢብኑል ቀይም ንግግር አጣሞ የፈሠረበት አሁን መጥቀስ አልችልም ረዝሟል፡፡

በሌላ ፅሁፍ እንገናኛለን፡፡ አሏህ ሃቅ ይግጠመን፡፡ ወልሃምዱሊላህ፡፡ 




Tuesday, August 25, 2020

፨ ስለ ዑለማዎች መታዘዝና የመሐይም ኸዋሪጆች ግንዛቤ 

=========================

፨ በአሏህ ሥም እጅግ በጣም ሩህሩህና እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው እጀምራለሁ፡፡

፨ በአህሉ ሡናዎች ዐቂዳ መሠረት የሚያከፍር መታዘዝ (الطاعة المكفرة) የሚባለው ነገር በልቁ የሚያዝ እንዳልሆነ ሙሐቂቅ ዑለሞቻችን ያስቀምጣሉ፡፡ ኸዋሪጆች ግን ከድሮም ጀምሮ ሱፈሃኡ-አህላም ናቸውና ሸሪዐን እንዴት መገንዘብ እንዳለባቸው የሚረዱ አይደሉም፡፡ የሚያከፍር መታዘዝ የሚባለው በኢስቲህላል ላይ የቆመ ነገር ነው፡፡


- ይህ ማለት በወንጀል ላይ ስንታዘዝ ሐላል በማድረግ ላይ ተመሥርተን የታዘዘን ከሆነ ብቻ እና ብቻ ነው ኩፍር አክበር የሚሆነው...

በተህሊል (ሐላል በማድረግ) እና በተሕሪም (ሐራም በማድረግ) ላይ መታዘዝ የሚባለው ነገር ኩፍር የሚሆነው በኢስቲህላል መልክ ከተፈፀመ ብቻ ነው፡፡ 


የአህሉ-ሡናህ ዑለሞች ይህን አንቀፅ በዚህ መልኩ ነው የተረዱና ያስቀመጡት! 


42:21 * ከሃይማኖት አላህ በእርሱ ያልፈቀደውን ለእነርሱ የደነገጉ ተጋሪዎች ለእነርሱ አልሏቸውን? * እንደዚሁ የአሏህ ንግግር ...

9:31 * ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለውን አንድን አምላክ ሊገዙ እንጂ ያልታዘዙ ሲኾኑ ሊቃውንቶቻቸውንና መነኮሳታቸውን፣ የመርየምን ልጅ አልመሲሕንም ከአላህ ሌላ አማልክት አድርገው ያዙ፡፡ ከሚያጋሩት ሁሉ የጠራ ነው፡፡* እናም 


6:121 *ብትታዘዙዋቸውም እናንተ በእርግጥ አጋሪዎች ናችሁ፡፡*


: {أم لهم شركاء شرعوا لهم من الدين ما لم يأذن به الله} وقوله تعالى : {وإن أطعتموهم إنكم لمشركون} وقوله تعالى : {اتخذوا أحبارهم ورهبانهم أربابا من دون الله} 


፨ እነዚህ አንቀፆች ሐላል በማድረግና ሐራም በማድረግ ላይ መታዘዝን በተመለከተ የሚያሥረዱ ናቸው፡፡ ይህ ነጥብ በሁለት መልኩ ተከፋፍሎ የሚታይ ነው፡፡ 


1ኛ).  በወንጀል ላይ መታዘዝ ይሆናል ይህ *ወንጀል* (معصية)ነው፡፡ 

2ተኛ). ወይ ደግሞ ኢስቲህላል በሚያደርግ ሁኔታ በወንጀል መታዘዝ የሚለው ነው፡፡ ይህ ከሽርክ ይመደባል፡፡ 


፨ ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ ረሂመሁሏህ እንዲህ ያብራራዋል

يقول ابن تيمية رحمه الله :

*ሌላን አካል በመሥማትና በመታዘዝ ከከፊል የአሏህ አምልኮቶች የተኩራራ ሠው እዚህ ቦታ ላይ *ላ ኢላሃ ኢለሏህ* የሚለውን ቃል አላረጋገጠም፡፡ እነዛ ቀሳውስቶቻቸውና መነኩሴዎቻቸው ጌታ አድርግ በመያዝ አሏህ ሐራም ያደረገውን ሃላል ሲሉ ፥ አሏህ ሐላል ያደረገውን እነሱ ሐራም ሲሉ የታዘዟቸው ሠዎች በሁለት በኩል ተከፋፍሎ የሚታይ ነው!


(من استكبر عن بعض عبادة الله سامعًا مطيعًا في ذلك لغيره، لم يحقق قول: لا إله إلا اللّه، في هذا المقام. وهؤلاء الذين اتخذوا أحبارهم ورهبانهم أربابا حيث أطاعوهم في تحليل ما حرم اللّه وتحريم ما أحل اللّه 👈🏼 يكونون على وجهين:


#أحدهما: أن يعلموا أنهم بدلوا دين اللّه فيتبعوهم على التبديل، #فيعتقدون تحليل ما حرم اللّه، وتحريم ما أحل اللّه، اتباعًا لرؤسائهم، مع علمهم أنهم خالفوا دين الرسل، فهذا كفر، وقد جعله اللّه ورسوله شركًا وإن لم يكونوا يصلون لهم ويسجدون لهم، #فكان_من_اتبع_غيره_في_خلاف_الدين مع علمه أنه خلاف الدين، #واعتقد ما قاله ذلك، دون ما قاله اللّه ورسوله مشركًا مثل هؤلاء.


፨ አንደኛው. እነሱ የአሏህ ዲን እንደቀየሩ ማወቃቸውና በዚያ በቀየሩት ነገር ሲከተሏቸው ነው፡፡ አለቆቻቸው በመከተል አሏህ ሐራም ያደረገውን ሐላል ነው ብለው #ሲያምኑ ፥ አሏህ ሐላል ያደረገውን ሐራም ነው ብለው #ሲያምኑ ነው፡፡ ይህ የሚሆነው የአሏህ ዲን የኻለፉ መሆናቸው ከማወቃቸው ጋር ነው፡፡ ይህ ክህደት ነው፡፡ አሏህና መልዕክተኛው ሽርክ አድርገውታል፡፡ ሠዎቹ (ለአለቆቻቸው) ባይሠግዱላቸውም እንኳን ፥ ከዲን በተቃራኒ ያለን ነገር  የተከተለ ሠው ፥ ከዲን የሚፃረር ነገር መሆኑ እያወቀ ከሆነ ፥ አሏህና መልዕክተኛው ከተናገሩት ውጪ በዚያ ነገር ላይ የተናገረውንም #ካመነ እንደነዚያ ሙሽሪክ ይሆናል፡፡ 


#والثاني: #أن_يكون_اعتقادهم وإيمانهم بتحريم الحلال وتحليل الحرام #ثابتًا، لكنهم أطاعوهم في معصية اللّه، كما يفعل المسلم ما يفعله من المعاصي التي يعتقد أنها معاص، فهؤلاء لهم حكم أمثالهم من أهل الذنوب)


፨ ሁለተኛው ፦ " ሐላሉን ሐራም በማድርግና ሐራሙን ሐላል በማድረግ ላይ ያላቸው እምነት የተረጋገጠ ነው፡፡ ነገር ግን አሏህን በማመፅ ነው የታዘዟቸው፡  ልክ አንድ ሙሥሊም ማንኛውም ወንጀል እንደሚሠራው ፥ ያ ወንጀል መሆኑን እያመነ የሚሠራው ነው ፥ እነዚህ ሠዎች እኔደ አምሳዮቻቸው የወንጀል ባለቤቶች አይነት ሁክም ነው ያላቸው፡፡ * 


📚


፨ ይህንን ነጥብ ይበልጥ በማብራራት እንመልከተው፡፡ ከሠለፎች የፀደቁ አሰሮችና የሙፈሲሮች ንግግር እየመጣን ፥ የስንኩል ግንዛቤ ባለቤቶች (ኸዋሪጆችን) እንምከር


፨ ኢማም አቡ ጃዕፈር አጥ-ጦበሪይ ረሂመሁሏህ እንዲህ ብሏል ፦ የአሏህን ንግግር [ ከአሏህ ውጪ ጌቶች አድርገው.. ] የሚለው (أربابا من دون الله) የሚለው ሲያብራራው እንዲህ ብሏል ፦ "ይህ ማለቱ ከአሏህ ውጪ ለነሡ አለቃ አደረጓቸው፡፡ #አሏህን_በማመጽ_ላይም_ይታዘዟቸዋል፡፡" አለ፡፡


يقول الإمام الطبري رحمه الله في تفسير قوله تعالى (أربابا من دون الله) : [ يعني: سادةً لهم من دون الله، #يطيعونهم_في_معاصي_الله]

፨ ይህ ንግግር ከቀልባችን አስተንትነን እንረዳው ፥ በርግጥ ኢማም አጥ-ጦበሪይ ማብራርያ አልጨረሰም፡፡ እንደ አንዳንድ ሱፈሃኡ-አህላም የሩጫ ግንዛቤ እቺን ቦታ ብቻ ቆረጠው ያመጧትና ባጢላቸውን ለመገንባት ይጣጣራሉ፡፡ ነገርግን ቀጥለን በደንብ የሚያብራራውን የኢማም አጥ-ጦበሪ ንግግር እናምጣው...


" (አለቆቻቸው) ሐላል ያደረጉትን ነገር ሐላል ነው ይላሉ ፥ በርግጥ አሏህ ሐራም አድርጎት እያለ፡፡ (አለቆቻቸው) ሐራም ያደረጉትን ሐራም ነው ይላሉ ፥ በርግጥ አሏህ ሐላል ካደረገው ነገር ሆኖ እያለ፡፡ " አለ ኢማም አጥ-ጦበሪይ ረሂመሁሏህ


[فيحلون ما أحلُّوه لهم مما قد حرَّمه الله عليهم، ويحرِّمون ما يحرِّمونه عليهم مما قد أحلَّه الله لهم]


፨ እዚህ ጋር ቆም ብለን የምናየው ነገር ቢኖር እነዚህ ሠዎች  ዑለሞቻቸው አሏህ ሃላል ያደረገውን ነገር  ሐራም ነው ሲሏቸው "አዎ ሃራም ነው" ሳይሉ ቢታዘዟቸውና ቢፈፅሙ ተግባራቸው ኩፍር አይሆንም፡፡ ባይሆን የማያከፍር ወንጀል ይሆንባቸዋል፡፡ ነገር ግን አሏህ ሐላል ያደረገውን ፥ አለቆቻቸው ሐራም ነው ሲሉ  *አዎ! ሐራም ነው* ብለው ከታዘዟቸው ይህ ጊዜ ኩፍር ይሆንባቸዋል፡፡ 


የኢማም አጥ-ጦበሪይ ሙሉው ንግግር ይኽ ነው፡፡👇

(يعني: سادةً لهم من دون الله، #يطيعونهم_في_معاصي_الله فيحلون ما أحلُّوه لهم مم


ا قد حرَّمه الله عليهم، ويحرِّمون ما يحرِّمونه عليهم مما قد أحلَّه الله لهم)


፨ ይቺ ነች የምታከፍር መታዘዝ በመባል የምትታወቀው፡፡ በወንጀል ስንታዘዝ ሐላል አድርገን ከታዘዝን ማለት ነው፡፡ 


ከዚህ በመቀጠል ኢማም አቡጃዕፈር ረሂመሁሏህ በተፍሢሩ ላይ የተለያዩ አሳሮች አምጥቶ ይህ የአህሉ ሡናህ ዐቂዳ ያጠናክረዋል፡፡ 


[16633- حدثني سعيد بن عمرو السكوني قال: حدثنا بقية، عن قيس بن الربيع, عن عبد السلام بن حرب النهدي, عن غضيف, عن مصعب بن سعد, عن عدي بن حاتم قال:


* ዐዲይ ቢን ሃቲም (ረዲየሏሁ ዐንሁ) እንዲህ አለ "የአሏህ መልዕክተኛ ሠለሏሁ ዐለይሒ ወሠለም ሡረቱል በራኣ እየቀሩ ሠማኋቸው፡፡ "ሊቃውንቶቻቸውንና መነኮሳታቸውን፣ የመርየምን ልጅ አልመሲሕንም ከአላህ ሌላ አማልክት አድርገው ያዙ፡፡ ከሚያጋሩት ሁሉ የጠራ ነው፡፡" (اتخذوا أحبارهم ورهبانهم أربابًا من دون الله) የሚለው ሲቀሩ "የአሏህ መልዕክተኛ ሆይ! እነሱ እኮ (ለሊቃውንቶቻቸውና ለመነኮሳቶቻቸው) አይሠግዱላቸውም ነበር፡፡ " አልኩኝ አለ፡፡ 


- እሳቸውም "እውነት ብለሃል ፣ ነገርግን አሏህ ሐራም ያደረገውን ነገር እነሱ (ሊቃውንቶችና መነኩሴዎቹ) ሐላል ያደርጉላቹህ ነበር፡፡ #እነዚያም_ሐላል_(ያደርጉታል)_ነው_ይላሉ፡፡ አሏህ ሐላል ያደረገውን እነሱ ሐራም ያደርጉታል፡፡ እነዚያም ሐራም (ያደርጉታል) ነው ይላሉ፡፡ " 


سمعت رسول الله صلى الله عليه وسلم يقرأ " سورة براءة "، فلما قرأ: (اتخذوا أحبارهم ورهبانهم أربابًا من دون الله)، قلت: يا رسول الله, إما إنهم لم يكونوا يصلون لهم! قال: صدقت, ولكن كانوا يُحلُّون لهم ما حرَّم الله #فيستحلُّونه, ويحرّمون ما أحلّ الله لهم فيحرِّمونه. (44)


፨ በዚህ የዐዲይ ቢን ሃቲም ረዲየሏሁ ዐንሁ ሐዲስ ላይ የተብራራው..

1ኛው). እነዚያ ጌታ አድርገው ያዙ የተባሉ ሠዎች ለሊቃውንቶቻቸውና ለመነኩሴዎቹ አይሠግዱላቸው ነበር፡፡ ያመልኳቸዋል የተባለው በሌላ አይነት እንደሆነ ረሡል ሠለሏሁ ዐለይሒ ወሠለም አብራሩለት፡፡ 


2ተኛ. እነዚያ ሠዎች አለቆቻቸው ጌታ አድርገው ያዙ የተባለው ፥ ሊቃውንቶቹና መነኩሴዎቹ ሃራምና ሃላል ብለው ሲነግሯቸው ፥ በወንጀል ስለታዘዟቸው ብቻ አይደለም፡፡ እንግዲያውስ አለቆቹ ሐላል ነው ፥ ሲሉ ተከታዮችም አዎ ሐላል ነው ብለው ይተገብሩ ስለነበር ነው፡፡ ይህ ለማረጋገጥ فيستحلُّونه በማለት በመዕሲያ ብቻ ስለታዘዟቸው እንዳልሆነ ገለፁ፡፡ 


፨ ሌላው የሠለፎች አሳር ፦ ከኹዘይፋህ የተዘገበ ነው፡፡ እሱም "ሊቃውንቶቻቸውንና መነኮሳታቸውን፣ የመርየምን ልጅ አልመሲሕንም ከአላህ ሌላ አማልክት አድርገው ያዙ፡፡ ከሚያጋሩት ሁሉ የጠራ ነው፡፡" ስለሚለው የአሏህ ቃል ተጠየቀ.. " ያመልኳቸው ነበርን?" ተብሎ ተጠየቀ፡፡


-እንዲህ መለሠ "አይ (አለቆቻቸው) ለእነሱ የሆነ ነገር ሐላል ያደረጉላቸው ጊዜ #እነሱም_ሐላል_ያደርጉታል፡፡ በእነሱ ላይ የሆነን ነገር ሐራም ያደረጉባቸው ጊዜ #ሐራም_ያደርጉት ነበር፡፡ " 


16634- حدثنا محمد بن بشار قال، حدثنا عبد الرحمن بن مهدي قال، حدثنا سفيان, عن حبيب بن أبي ثابت, عن أبي البختري, عن حذيفة: أنه سئل عن قوله: (اتخذوا أحبارهم ورهبانهم أربابًا من دون الله)، أكانوا يعبدونهم؟ قال: لا كانوا إذا أحلُّوا لهم شيئًا #استحلوه, وإذا حرَّموا عليهم شيئًا حرَّموه.


በዚህ 👇 ዘገባ ደግሞ ለኹዘይፋህ እንዲህ ተባለ " ሊቃውንቶቻቸው ያዙ  ..."( اتخذوا أحبارهم) ስለሚለው የአሏህ ቃል ምን ትላለህ?" ተባለ፡፡ እንዲህ አለ "እነሱማ ለነሱ ብለው አይፆሙላቸውም ፥ አይሠግዱላቸውም ነበር፡፡ ነገርግን ለነሱ አንድ ነገር ሐላል ሲያደርጉላቸው (እነሱም) #ሐላል ይሉ ነበር፡፡ አሏህ ሃላል ያደረገላቸው ነገር ሆኖ (አለቆቻቸው) ሐራም ነው ሲሉ እነሱም #ሐራም ነው ይላሉ፡፡ በዚህ መልኩ ነበር ጌታ ተደርገው የመያዛቸው ነገር፡ " 


16636- حدثنا ابن وكيع قال، حدثنا يزيد بن هارون, عن العوام بن حوشب, عن حبيب عن أبي البختري قال: قيل لحذيفة: أرأيت قول الله: (اتخذوا أحبارهم) ؟ قال: أمَا إنهم لم يكونوا يصومون لهم ولا يصلون لهم, ولكنهم كانوا إذا أحلوا لهم شيئًا #استحلُّوه, وإذا حرّموا عليهم شيئًا أحله الله لهم حرَّموه, فتلك كانت رُبوبيَّتهم.]


፨ እዚህ በተጨማሪ የሚባለው ወደ-ጧጉት መፋረድ ኩፍር የሚሆነው በኢስቲህላል መልክ ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱም ወደጧጉቱ ተሃኩም አደርግን ማለት በሚፈርድበት ነገር #ታዘዝነው ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ተሃኩም (التحاكم) መሠረቱ መታዘዝ ነው፡፡ 


ለዚህም ነው አሏህ ሱብሃነሁ ወተዐላ ለነዚያ ሙናፊቆች ሲወቀሳቸው *መታዘዝን በተመለከተ ርዕስ ላይ ነው፡፡* ምክንያቱም መታዘዝ ነው የተሃኩም መሠረቱ፡፡ ይህ ማለት በአንድ መሥዐላ ላይ አ


ሏህን በቀልብና በሠውነታችን በምንሠራው ተግባር ለመታዘዝ  የአሏህን ሑክም መፈለግ ማለት ነው ተሃኩም ሲባል፡፡ 


አሏህ እነዚያ ሙናፊቆችን ሲወቅሳቸው የተናገረውን እንይ

: {وَمَا أَرْسَلْنَا مِن رَّسُولٍ #إِلَّا_لِيُطَاعَ_بِإِذْنِ_اللَّهِ ۚ وَلَوْ أَنَّهُمْ إِذ ظَّلَمُوا أَنفُسَهُمْ جَاءُوكَ فَاسْتَغْفَرُوا اللَّهَ وَاسْتَغْفَرَ لَهُمُ الرَّسُولُ لَوَجَدُوا اللَّهَ تَوَّابًا رَّحِيمًا}


[ ማንንም መልክተኛ በአላህ ፈቃድ ሊታዘዙት እንጅ አልላክንም፡፡ እነሱም ነፍሶቻቸውን በበደሉ ጊዜ ወደ አንተ ቢመጡና አላህንም ምሕረትን በለመኑ መልክተኛውም ለነርሱ ምሕረትን በለመነላቸው ኖሮ አላህን ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ኾኖ ባገኙት ነበር፡፡ ] 4:64

يقول الإمام الطبري رحمه الله :

፨ ኢማም አጥ-ጦበሪይ ረሂመሁሏህ እንዲህ ይላል ፦ " ይህ ከአሏህ ዘንድ የሆነ ማሥፈራርያ ነው፡፡ ለነዚያ ተሃኩምን ፈልገው የሄዱትን፡፡ እነሱ በነብዩ ሠለሏሁ ዐለይሒ ወሠለም ላይ በተወረደው አምነናል ብለው ይሞግቱ ነበር፡፡ ወደጧጉትም በመካከላቸው ባለው ጉዳይ ሊፋረዱ ሄዱ ፥ ከረሡል ሠለሏሁ ዐለይሒ ወሰለም እየሸሹ፡፡" ለነሱ አሏህ እንዲህ ይላቸው: አንድም መልዕክተኛ አልላኩም ፥ ወደሱ በላኩት ነገር ላይ እንዲታዘዙት ግዴታ ባደርግ እንጂ፡፡ ሙሐመድ ሠለሏሁ ዐለይሂ ወሠለም ከነዚያ ሩሡሎች መካከል ነው፡፡ እሳቸውን መታዘዝና ሑክማቸውን መውደድ የተወ ሠው ፥ ከዚያ ወደጧጉት ሄዶ የተፋረደ የኔን ትዕዛዝ ጥሷል፡፡ ግዴታ ያደረግኩት ነገርም አጠፋ፡፡ " 




(وإنما هذا من الله #توبيخ للمحتكمين من المنافقين = الذين كانوا يزعمون أنهم يؤمنون بما أنـزل إلى النبي صلى الله عليه وسلم = فيما اختصموا فيه إلى الطاغوت، صدودًا عن رسول الله صلى ال


له عليه وسلم. يقول لهم تعالى ذكره: ما أرسلتُ رسولا إلا #فرضت_طاعته على من أرسلته إليه، فمحمد صلى الله عليه وسلم من أولئك الرسل، #فمن_ترك_طاعته_والرِّضى_بحكمه_واحتكم_إلى_الطاغوت، فقد خالف أمري، وضيَّع فرضي.)

📚 አጥ-ጦበሪ


፨ ስለተሃኩም ሲወራ አስሉ መሠረቱ ከጧዐ (መታዘዝ) የሚመደብ ነገር ነው፡፡ 


፨ስለዚህ በሌላ ክፍል እንመጣበታለን፡፡ ዋናው የተፈለገው መልዕክት ዑለማዎች ፥ ሊቃውንቶች ፥ መነኩሴዎች የመሳሰሉት ያለ ኢስቲህላል ሐራምና ሐላል ብለው ከአሏህ ኪታብ ውጪ በሚሉት ነገር መታዘዝ  ትልቁ-ኩፍር አይደለም፡፡


🔖 ወልሐምዱሊላሂ ረቢል ዐለሚን

Monday, August 24, 2020

ስለ-ተሃኩም በተመለከተ የሡረቱ ኒሳእ ፡61 አንቀፅ ማብራርያ

🔖 በአሏህ ሥም እጅግ በጣም ሩህሩህና እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው እጀምራለሁ፡፡  

በዚህ ሁፍ በአሏህ እርዳታ በመታገዝ ወደ ጧጉት መፋረድ ምን እንደሆነ እና ወደ ጧጉትም መፋረድ ያለው ሁክም እንመለከታለን፡፡ በምን አይነት ሁኔታ ወደ ተሃኩም መፋረድ ኩፍር አክበር የሚሆነው? እናያለን፡፡ 


🔖 ይህ አንቀፅ የወረደባቸው ሠዎች ክህደት ያገኛቸው ወደ ጧጉት በመፋረዳቸው ብቻ ነውን ወይስ የጧጉትን ሁክም ከአሏህ ሁክም የበለጠ ፥ ወይም እኩል የሆነ ፥ ወይም ኢስቲህላል ያደርጉም ስለነበር ነው ፥ ወይስ  በአሏህ ሁክም አይወዱም ነበር?


  እዚህ ቦታ ንግግራችን ሁሉ ሊሽከረከርበት የሚችልበትን ሁለት መግቢያ አስቀድመን የምንመለከት ይሆናል፡፡ 


#የመጀመርያው).  በዚህ አንቀፅ ላይ ተሃኩም ያደረጉት ሠዎች ትክክለኛው ተግባራቸው ምን እንደነበረ ማረጋገጥ፡፡ 


#ሁለተኛው) .እነዚያ ሠዎች በትክክል ይተገብሩ የነበረው #ተግባራቸው ከዑለሞች በማረጋጥ እንመለከታለን፡፡ 


ይህ አሁን በዝርዝር የምንመለከተው መስዐላ *አሏህ ባላወረደው ነገር መፍረድ* የሚለው ውስጥ ሊካተት የሚችል ነገር ነው፡፡ ይህ ጉዳይ ሠለፎች ዘንድ እንኳን በተቅኒን ደረጃ ተከስቷል፡፡ በታብዕዮች ዘመን ሙኩስ የተባለን በሸሪዐ የሌለ ህግ አውጥተው ያስተዳድሩ ነበር፡፡ በኒ ኡመዮችን በዚህ ያከፈራቸው አንድም የለም፡፡ ( አንዳንዶች ይህ ሲባል በዘመናችን ያሉ የአሏህን ሁክም የመለሱ ፥ ኢስላማዊ መንግስት ኋላቀርነት ነው የሚሉ ፥ ኢስቲህላልና ሌሎችም ኩፍርያት የሆኑ ነገሮች የሞሉበት *ዲሞክራሲያዊ* ሥርዐት አራማጆችን እንዲሁም በሙሥሊሞች ካፊርን እያገዙ ያሉ ሙርተዶችን በዚህ ርዕስ የሚመደቡ ይመሥላቸዋል፡፡ ነገሮቹ ልዩነታቸው ለማወቅ የዑለሞች ትክክለኛ መንሐጅ ይዘን ራሳችን ከጥመት ተጣሪዎች መጠበቅ ይኖርብናል፡፡ 


፨ በቀጥታ ወደ አንቀፁ ማብራርያ ስንገባ ልብ ብለን መረዳት ያለብን ነገር ይኖራል፡፡ 

1ኛ). ተሃኩም ማድረጋቸው የኒፋቃቸው ምልክት እንደነበር

2ኛ). ተሃኩም አድርገው የነበረው የአሏህ ሁክም ከመፈፀም ኩራት ይዟቸው (በኢስቲክባር) እንደነበር እና የአሏህ ሑክምን ወደው የሚቀበሉ ስላልነበሩ ነው ክህደት ላይ የወደቁት.. 


በመጀመርያ አንቀፁን እናቅርበው፡፡ ትክክለኛ የኩፍራቸው ሁኔታ እንዴት እንደነበረና አሏህም ምን አይነት ሁክም እንደወሠነባቸው እንይ፡፡


፨ አሏህ የሙናፊቆችን ሁኔታ እንዲህ በማለት ይነግረናል፡፡ አስተንትነት እናንብበው፡፡


4:61* ወደ እነዚያ እነርሱ በአንተ ላይ በተወረደውና ከአንተ በፊትም በተወረደው አምነናል ወደሚሉት፤ አላየህምን በእርሱ እንዲክዱ በእርግጥ የታዘዙ ሲኾኑ ወደ ጣዖት መፋረድን ይፈልጋሉ፡፡ ሰይጣንም (ከእውነት) የራቀን መሳሳት ሊያሳስታቸው ይፈልጋል፡፡ * 


قال الله تعالى : {ألم ترَ إلى الذين يزعمون أنهم آمنوا بما أنزل إليك وما أنزل من قبلك يريدون أن يتحاكموا إلى الطاغوت وقد أمروا أن يكفروا به ويريد الشيطان أن يضلهم ضلالا بعيدا 


4:65 * ለእነርሱም፡- «አላህ ወደ አወረደው (ቁርኣን)ና ወደ መልክተኛው ኑ» በተባሉ ጊዜ መናፍቃን ከአንተ መሸሽን ሲሸሹ ታያቸዋለህ፡፡*


وإذا قيل لهم تعالوا إلى ما أنزل الله وإلى الرسول رأيت المنافقين #يصدون_عنك_صدودا


4:66 * እጆቻቸውም ባስቀደሙት (ጥፋት) መከራ በደረሰችባቸውና ከዚያም «ደግን ሐሳብና ማስማማትን እንጅ ሌላ አልሻንም» በማለት በአላህ የሚምሉ ኾነው በመጡህ ጊዜ እንዴት ይኾናሉ? *


فكيف إذا أصابتهم مصيبة بما قدمت أيديهم ثم جاؤك #يحلفون_بالله_إن أردنا إلا #إحسانا_وتوفيقا ,  

* እነዚህ እነዚያ አላህ በልቦቻቸው ውስጥ ያለውን ሁሉ የሚያውቅባቸው ናቸው፡፡ እነርሱንም ተዋቸው ገሥጻቸውም፡፡ ለእነርሱም በነፍሶቻቸው ውስጥ ስሜት ያለውን ቃል ተናገራቸው፡፡ *

أولئك الذين يعلم الله #ما_في_قلوبهم  #فأعرض_عنهم وعظهم وقل لهم في أنفسهم قولا بليغا}


.................. ሙሉ አንቀፁ ይህ ይመሥላል፡፡ በዚህ አንቀፅ መነሳት የሚኖርባቸው ወሳኝ ነጥቦች እያየን እንቀጥላለን፡፡


1ኛው). አሏህ እንደሚጠቅስልን እነዚህ ሠዎች ፥ አሏህ ካወረደው ኪታብ (ሑክም) ይሸሻሉ፡፡ ይህ ማለት ከአሏህ ሁክም ይሸሻሉ (ኢዕራድ ያደርጋሉ) ማለት ነው፡፡ 


፨ ኢብኑል ሙንዚር ተፍሢሩ ላይ እንደመጣው ፦

جاء في تفسير إبن المنذر :

1949 - حَدَّثَنَا زكريا، قَالَ: حَدَّثَنَا أَبُو جعفر مُحَمَّد بْن أحمد بْن نصر، قَالَ: حَدَّثَنَا يوسف بْن عدي، قَالَ: حَدَّثَنَا رشدين، عَنْ يونس بْن يزيد، عَنْ عطاء، فِي قول الله جل ثناؤه "{يَصُدُّونَ عَنْكَ صُدُودًا} ، قَالَ: الصدود: الإعراض "


በዚህ ሠነድ ላይ ታብዒዩ ዐጧእ ( ረሂመሁሏህ) * ከአንተ መሸሽን ሲሸሹ ታያቸዋለህ፡፡* (يَصُدُّونَ عَنْكَ صُدُودًا) የሚለው ሲተረጉም *አስ-ሱዱድ* (الصدود)  የተባለው መሸሽ ኢዕራድ (الإعراض) ነው ብሏል፡፡ 📚 ተፍሢር ኢብኑል ሙንዚር


፨ ኢብኑ ከሢር ረሂመሁሏህ ተፍሢሩ ላይ እንዲህ አስቀምጧል፡፡

- وفي تفسير ابن كثير

"( يصدون عنك صدودا ) أي : يعرضون عنك #إعراضا_كالمستكبرين عن ذلك."

* " ከአንተ መሸሽን ሲሸሹ ታያቸዋለህ" ( يصدون عنك صدودا ) የሚለው ማለት የተፈለገው * እንደኩራተኞች (كالمستكبرين) በመሆን ካንተ መሸሽን ይሸሻሉ፡፡* ብሎ አስቀምጧል፡፡ እንግዲህ ሙናፊቆቹ ኢስቲክባር (መኩራት) እንደነበረባቸው ግልፅ ሆነ ማለት ነው፡፡ 


፨ እንደሚታወቀው አል-ኢስቲክባር (والاستكبار) የኢብሊስ ክህደት አይነቶች ሥር የሚገባ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ የኢብሊስ ኩፍር ኢስቲክባር (መኩራት) የነበረበት ነው፡፡ እነዚህ ሙናፊቆችም ይህን *ኢስቲክባር* የተጠናወታቸው ነበሩ፡፡ "መፋረድን መተው" ብቻ የሚመለከት ነገር አልነበረም፡፡ 


-አንድ ሠው በአሏህ ሁክም የዝሙትን ሐራምነት ላይ ኩራት ይዞት ፥ ዝሙት ቢፈፅም ካፊር ይሆናል፡፡ ነገርግን ያለኩራት ዝሙት የፈፀመ እንደሆነ ካፊር አይሆንም፡፡ የነዚህ ሙናፊቆችም " መፋረድን መተዋቸው" ብቻ አልነበረም ለዚህ የዳረጋቸው *ኢስቲክባር* ስለነበረባቸው ነው፡፡ 


፨ ሙቃቲል ቢን ሡለይማን 📚 ተፍሢር ላይ እንዲህ ይገልፀዋል፡፡ 

* ከአንተ መሸሽን ሲሸሹ ታያቸዋለህ * (يصدون عنك صدودا) የሚለውን ፥ ማለት የተፈለገበት "አንተ ሙሃመድ ሆይ! ካንተ ውጪ ወደሆነ አካል መሸሽን ይሸሻሉ፡፡ ይህ ያደረጉት በፍርድ ላይ እንዳትበድላቸው በመፍራት ነው፡፡ * 📚 ተፍሢር ሙቃቲል

- وفي تفسير مقاتل بن سليمان

"(يصدون عنك صدودا)  يعني يعرضون عنك يا محمد إعراضا إلى غيرك، #مخافة_أن_تحيف_عليهم" 


፨ እነዚህ ሙናፊቆች ከረሡል ﷺ በኩል በደል ይደርስብናል ፥ ይበድለናል ብለው በራሳቸው ላይ ይፈሩ ነበር፡፡ ምንም ጥርጥር የሌለው ነገር የኢሥላም ሸሪዐህ ፍትሐዊ እንደሆነና በደል እንደሌለበት የማያምን ሠው ካፊር ነው፡፡


-2ተኛው). አሏህ ስለነዚህ ሙናፊቆች ሲገልፅ ፥ እነሱ በአሏህ ይምሉ ነበር፡፡ እነሱ (በዚህ ተሃኩም ፈልጋ ወደሌላ መሄዳቸው) «ደግን ሐሳብና ማስማማትን እንጅ ሌላ አልሻንም» በማለት ነበር፡፡ አሏህ ሡብሃነሁ ወተዐላ ግን በቀልቦቻቸው የያዙት የደበቁትን ያውቅ ነበር፡፡ ይህ በዋናነት ከሚሠጠን ማሥረጃ መካከል ፥ እነዚህ ሙናፊቆች በውስጣቸው ካለ የተለየ ነገር በውጭ ገፅታቸው ያሳዩ ነበር፡፡ በውስጣቸው ኒፋቅ ነበር፡፡ 


፨ ኢብኑ ዘመነይን እንዲህ ብሏል ፦


قال ابن زمنين :

(فكيف إذا أصابتهم مصيبة) قال الحسن : وهذا كلام منقطع عما قبله وعما بعده ؛ يقول : (إذا أصابتهم) يعني : #أن_يظهروا_ما_في_قلوبهم_فيقتلهم رسول الله - صلى الله عليه وسلم - 


*መከራ በደረሰችባቸውና ከዚያም «ደግን ሐሳብና ማስማማትን እንጅ ሌላ አልሻንም» በማለት በአላህ የሚምሉ ኾነው በመጡህ ጊዜ እንዴት ይኾናሉ* የሚለው ላይ (فكيف إذا أصابتهم مصيبة) "መከራ ባጋጠማቸው ጊዜ እንዴት ይኾናሉ" የሚለው የአሏህ ንግግር ከፊትና ከኋላ ካለው ንግግር የተቋረጠ ነው፡፡ *ባገኛቸው ጊዜ * ሲል በቀልቦቻቸው የደበቁትን ግልፅ ባደረጉ ጊዜ ረሡል ይገድሏቸዋል፡፡ ማለት ነው፡፡ 


(ثم جاءوك يحلفون بالله إن أردنا إلا إحسانا وتوفيقا) أي :

#إن_أردنا_إلا_الخير .(أولئك الذين يعلم الله ما في قلوبهم) : #من_الشرك_والنفاق}

* ከዚያም «ደግን ሐሳብና ማስማማትን እንጅ ሌላ አልሻንም» በማለት በአላህ የሚምሉ ኾነው በመጡህ ጊዜ እንዴት ይኾናሉ* ማለቱ  መልካምን እንጂ ሌላ ፈልግን አይደለም አሉ፡፡ * እነዚህ እነዚያ አላህ በልቦቻቸው ውስጥ ያለውን ሁሉ የሚያውቅባቸው ናቸው፡፡ እነርሱንም ተዋቸው ገሥጻቸውም፡፡ ለእነርሱም በነፍሶቻቸው ውስጥ ስሜት ያለውን ቃል ተናገራቸው፡፡ *


📚 ተፍሢር ኢብኑ ዘመነይን


፨ እንደዚሁም ሙናፊቆቹ በውጣቸው ያለው ሌላ ፥ በውጭ ገፅታቸው የሚያሳዩት ሌላ እንደሆነ ከሚጠቁሙት መካከል 

وفي تفسير البغوي : 

"( أولئك الذين يعلم الله ما في قلوبهم ) من النفاق ، أي : #علم_ان_ما_في_قلوبهم #خلاف_ما_في_ألسنتهم"


[ አል-በገዊ ፦ እንዲህ ብሏል *እነዚያ አላህ በልቦቻቸው ውስጥ ያለውን ሁሉ የሚያውቅባቸው ናቸው፡፡* ከነፍቅና የተነሳ ይህ በሚለው የተፈለገበት በቀልባቸው የቋጠሩት ፥ በምላሳቸው ከሚሉት ተቃራኒ ነው፡፡ 

وفي تفسير الحافظ عز الدين الرسعني الحنبلي : 

፨ ዒዘዲን አርረሥዐኒ አልሃንበሊ በተፍሲሩ እንዲህ ብሏል ፦


* እጆቻቸው ባስቀደመው (ጥፋት)*  ሲል አሏህ #ኒፋቃቸው እና #ወደ_ጧጉት_መፋረዳቸውን_ነው፡፡ *ደግን ሐሳብና ማስማማትን እንጅ ሌላ አልሻንም* ሲሉ ደግሞ ማለት የፈለጉት መልካም ነገር ፥ ሐቅን የሚገጥም ነገር በመፈለግ ነው፡፡ ማለታቸው ነው፡፡ በሌላም እንደተባለው * ከአንተ ውጪ ወደ አለ ሄደን መፋረድ አልፈለግንም በሁለቱ ተከራካሪዎች ዘንድ መልካም ነገርና ማስማማት እንጂ፡፡* ይላሉ፡፡ የአንተን ሑክም ለመቃረን ብለን ወይም ባንተ ፍርድ ወደን የማንቀበል ሆነን አይደለም፡፡ #ይህ_ከነሱ_የሆነ_ውሸት_ነው፡፡ አታይምን አሏህ የሚለውን *እነዚያ አላህ በልቦቻቸው ውስጥ ያለውን ሁሉ የሚያውቅባቸው ናቸው፡፡* በልቦቻቸው ያለው ሲል ኒፋቅና ኩፍር ፥ እንዲሁም ከደበቁት ተቃራኒ ነገር ግልፅ ማድረጋቸውን ነው፡፡ ]


[( بما قدمت ايديهم ) #من_النفاق_والتحاكم_إلى_الطاغوت .

( إلا إحسانا وتوفيقا ) اي : #خيرا_وطلبا #لما_يوافق_الحق .

وقيل : #ما_اردنا_بالتحاكم إلى غيرك #إلا_إحسانا_وتوفيقا #بين_الخصمين #لا_مخالفة_حكمك #وعدم_الرضى_بقضائك #وذلك_كذب_منهم ، ألا تراه يقول ( أولئك الذين يعلم الله ما في قلوبهم ) يعني #من_الكفر_والنفاق #وإضمارهم_خلاف_ما_يبطنون .} 

📚ተፍሢር ዒዘዲን


፨ ሙፈሢሩ ኢብኑ ከሢር ረሂመሁሏህ እንዲህ ብሏል ፦* እነዚህ እነዚያ አላህ በልቦቻቸው ውስጥ ያለውን ሁሉ የሚያውቅባቸው ናቸው፡፡ እነርሱንም ተዋቸው ገሥጻቸውም፡፡ ለእነርሱም በነፍሶቻቸው ውስጥ ስሜት ያለውን ቃል ተናገራቸው፡፡ * ሲል አሏህ ማለት የተፈለገው " ወደ አንተ ዑዝራቸውን ያቀርባሉ፡፡ ይምላሉም፡፡ " እኛ ካንተ ውጪ በመሄዳችን ፥ ካንተ ውጪ ወደሆነ አካል መፋረዳችን ደግን ሐሳብንና ማስማማትን እንጂ ሌላ ፈልገን አይደለም ይላሉ፡፡ እንዲሁ በውጪ ገጽታ ለማሥመሠል ብለን እንጂ ከውስጣችን እዛ ያለው ፍርድ አምነንበት አይደለም፡፡ " ይላሉ፡፡ 


وفي تفسير ابن كثير [ (ثمّ جاءوك يحلفون باللّه إن أردنا إلا إحسانًا وتوفيقًا) أي: يعتذرون إليك ويحلفون : ما أردنا بذهابنا إلى غيرك، #وتحاكمنا_إلى_عداك إلّا إلإحسان والتوفيق ، أي: #المدارة_والمصانعة، #لا_إعتقادا_منا #صحة_تلك_الحكومة،]


፨ እነሡ ውሸታቸውን እኛ የአሏህን ሑክም እንወዳለን ብለው ይሞግታሉ፡፡ በአሏህ ሁክም ወደው የሚቀበሉ አይደሉም፡፡ እንደውም የአሏህ ሁክም ትክክለኝነት አይቀበሉም፡፡


3ተኛው). አሁን ወደ ዋናው ነጥብ መጥተናል፡፡ በመጨረሻም አሏህ ስለነዚህ ሠዎች ሲናገር እንዲህ ነበር ያለው ፦

{فأعرض عنهم وعِظْهم وقل لهم في أنفسهم قولاً بليغاً} 

*እነርሱንም ተዋቸው ገሥጻቸውም፡፡ ለእነርሱም በነፍሶቻቸው ውስጥ ስሜት ያለውን ቃል ተናገራቸው፡፡* አለ አሏህ፡፡


፨ይህ የጌታችን ትዕዛዝ ብቻውን ወደ ጧጉት መፋረድ ብቻውን ኩፍር አክበር ነው ፥ ከኢስላም ያስወጣል የሚሉ ሠዎችን  መሠረት ለማውደም በቂ ይሆን ነበር፡፡ 


፨ ልብ በል ‼️እነዚህ ሙናፊቆች በገሃድ የሠሩት ሥራ [ ከሸሪዐ ውጪ ወደ ሆነ ነገር መፋረድ ብቻ ] ሆኖ ፥ ያለምንም ኢስቲክባር ፥ ኢስቲህላል ኩፍር አክበር ነው ቢባል ኖሮ ፥ አሏህ መልዕክተኛውን (ሠለሏሁ ዐለይሂ ወሠለም) *ኢስቲታባ* እንዲያርጓቸው ያዝ ነበር ወይም ከኩፍር ተውበት እንዲያደርጉ አለበለዚያ እንደገደሉ ያደርግ ነበር፡፡


- የኩፍር አህካሞችን በነዚህ ሠዎች እንዲፈፀም ባደረጉ ነበር ፥ ነገር ግን አሏህ ረሡልን *ተዋቸው ነው ያላቸው ፥ ከነሱ እንዲሸሹ ነው የነገራቸው፡፡ * ምክንያቱ ምንድነው ከተባለ አሏህ ለረሡል ሠለሏሁ ዐለይሒ ወሠለም የነዚህ ሠዎች ውስጣዊ ምንነታቸው አሳወቃቸው፡፡ እነዚህ ሠዎች ወደጧጉት ሲፋረዱ ፥ በጧጉቱ ሁክም ወደው እንደሆነ ፥ የጧጉቱ ሑክም ከአሏህና መልዕክተኛ ሑክም የተሻለ ነው ብሎ እንደሄዱ ወይም ከአሏህ ሁክም እኩኩል ነው ብለው በማሠብ ሄደው እንደተፋረዱ አሳወቃቸው፡፡ ከላይ በውጪ ገፅታቸው የሚያሳዩት በውስጣቸው ካለው የተቃረነ ነበር፡፡ በውኮጣቸው አምቀው የያዙት ነገር ግልፅ ቢያደርጉ ኖሮ የአሏህ መልዕክተኛ በተጋደሏቸው ነበር፡፡ ምክንያቱም *ሙርተድ* ሆነው ነበር እና፡፡ 


፨ ኢብኑ ዘመነይን እንዲህ ብሏል ፦

قال بن زمنين :

" (أولئك الذين يعلم الله ما في قلوبهم) : #من_الشرك_والنفاق

(فأعرض عنهم) : #فلا_تقتلهم #لما_جعلوا #يظهر


ون_الإيمان 

(وعظهم وقل لهم في أنفسهم قولا بليغا) يقول لهم : #إن_أظهرتم_ما #في_قلوبكم_قتلتكم ."

* እነዚያ አላህ በልቦቻቸው ውስጥ ያለውን ሁሉ የሚያውቅባቸው ናቸው* የሚለው አንቀፅ ሽርክና ኒፋቅ ማለቱ ነው፡፡ *ከነሱ መሸሽን ሽሽ* (فأعرض عنهم) የሚለው ደግሞ #ኢማንን_ግልፅ_እያደረጉ_ሥለሆነ_አትግደላቸው_ማለቱ ነው፡፡ *እነርሱንም ተዋቸው ገሥጻቸውም፡፡ ለእነርሱም በነፍሶቻቸው ውስጥ ስሜት ያለውን ቃል ተናገራቸው፡፡ * የሚለው ቃል ደግሞ  #በቀልቦቻቹህ_ውስጥ_ያለውን_ግልፅ_ካደረጋቹህ_ትገደላላቹህ፡፡ " እያላቸው ነው፡፡ 


✅ ይህ ወደጧጉት ተሃኩም ማድረግ ብቻውን ኩፍር አክበር እንዳልሆነና ሙናፊቆቹም ኩፍር የሚወድቅባቸው በቀልባቸው በቋጠሩት እንደሆነ አንቀፁ በደንብ ይገልፃል፡፡ 


፨ ሙፈሲሩ አል-በገዊ እንዲህ ብሏል ፦

ويقول البغوي : 

"( فأعرض عنهم ) أي : عن عقوبتهم وقيل : فأعرض عن قبول عذرهم وعظهم باللسان ، وقل لهم قولا بليغا ، وقيل : هو التخويف بالله ، وقيل : أن توعدهم بالقتل إن لم يتوبوا ، قال الحسن : القول البليغ أن يقول لهم : #إن_أظهرتم #ما_في_قلوبكم #من_النفاق_قتلتم لأنه يبلغ من نفوسهم كل مبلغ"

*ከነሱ ሽሽ(ራቅ)* የሚለው የተፈለገበት እነሱ ከመቅጣት ራቅ ማለት ነው፡፡ በሌላም እንደተባለው *ዑዝራቸውን ከመቀበል ራቅ፡፡ በአንደበትህ ገስፃቸው፡፡ *ለእነርሱም በነፍሶቻቸው ውስጥ ስሜት ያለውን ቃል ተናገራቸው* የሚለው ደግሞ ይህ በአሏህ እንዲያሥፈራራቸው ነው፡፡ በሌላ እንደተባለው ደግሞ ተውበት ካላደረጉ ፥ ትገድላቸዋለህ እንደማለት ነው፡፡ አል-ሐሰን እንዲህ ብሏል ፦* ስሜት ያለው ቃል* ሲል እንዲህ እንዲላቸው ነው [ በቀልባቹህ ውስጥ ያለ ኒፋቅ ግልፅ ካደረጋቹህ ትገደላላቹህ፡፡ 

ويقول الرسعني الحنبلي : 

፨ ዒዘዲን አርረሥዐኒ አልሃንበሊ  እንዲህ ብሏል ፦

" ከነሱ ሽሽ(ራቅ) * የሚለው አያ ቅጣታቸውን ተውላቸው ማለት ነው፡፡ *ለእነርሱም በነፍሶቻቸው ውስጥ ስሜት ያለውን ቃል ተናገራቸው፡፡* የሚለው ደግሞ ለነሱ ተናገራቸው ፥ በሐይልም ገስፃቸው፡፡ በነፍሶቻቸው ተፅዕኖ ሊያሳድር የሚችል ግሳፄ አድርግላቸው፡፡* ማለት ነው፡፡ አልሐሰን አልበስሪ እንዲህ ብሏል ፦ "ለነሱ ተናገራቸው ማለቱ  *በቀልቦቻቹህ ያለውን ኒፋቅ ግልፅ ብታደርጉ ትገደላላቹህ* እየተባሉ ነው፡፡

" (فأعرض عنهم ) دع عقوبتهم .

( وقل لهم في أنفسهم قولا بليغا ) : قل لهم وبالغ في وعظهم مبالغة تؤثر في نفوسهم وتبلغ كنه قلوبهم ، قال الحسن البصري - رحمه الله -  المعنى : قل لهم :   #إن_أظهرتم #ما_في_قلوبكم #من_النفاق_قتلتم"


📚ተፍሢር አርረሥዐኒ


፨ ኢብኑ ከሢር እንዲህ ብሏል ፦

ويقول الحافظ بن كثير 

* ከእነሱ ራቅ(ሽሽ) * የሚለው ይህ ማለት በቀልባቸው ውስጥ ባለ ነገር አትጨክንባቸው (ሺዳህ አታሳያቸው)፡፡ ገስፃቸው የሚለው ደግሞ በቀልቦቻቸው ውስጥ ካለ ኒፋቅና የውስጥ ሸር ከልክላቸው፡፡ * እያለ ነው፡፡ 

"ولهذا قال له: (فأعرض عنهم) أي: #لا_تعنفهم #على_ما_في_قلوبهم (وعظهم) أي: #وانههم_على_ما #في_قلوبهم #من_النفاق_وسرائر_الشر"

📚 ተፍሢር ኢብኑ ከሢር


‼️ እዚህ ወሳኝ ነጥብ አለ፡፡ ይህች አንቀፅ የወረደችው እነዚያ ሠዎች በውጣቸው የካዱ እንደነበሩ ለመግለፅ ነው፡፡ ያደረጉት ተሃኩም ወይም ወደጧጉት ሄደው ፍርድ የፈለጉበት ገፅታም #አምነውበት ነበር ሄደው የተፋረዱት፡፡ ግን ያንን ግልፅ አላደረጉም፡፡ ነገርግን ቁርኣን ነው በውስጣቸው ያለውን ኩፍር ለረሡል ሠለሏሁ ወለይሒ ወሠለም ያጋለጠው፡፡ 


፨ ይህ ነው እንግዲህ የቁርኣኑ አንቀፅ አገባብ ፥ ከዕውቀት ባለቤቶች ተፍሢር ጋር ፡፡ እነዚህ ሙናፊቆች በአሏህ ሑክም ላይ ኩራት የሚይዛቸው (ሙስተክቢሪን) ነበሩ፡፡ የጧጉቱንም ህግ ከአሏህ ህግ ያስበልጡ ነበር፡፡ ይህ የዕውቀት ባለቤቶች ያረጋገጡ ሐቅ ነው፡፡ ጃሒሎች ቢስቱትም፡፡ ወደ ጧጉቱ ሄደው የተፋረዱበት ሁኔታም አስቀምጠዋል፡፡ 


‼️ለምሳሌ ኢማም አቡ ጃዕፈር አጥጦበሪ ረሂመሁሏህ ተፍሢሩ ላይ እንዲህ ብሏል ፦

يقول الإمام الطبري رحمه الله في تفسيره الآية :

[ *የልቅናው ባለቤት አሏህ በዚህ ንግግሩ ማለት የፈለገው * አንተ ሙሃመድ ሆይ! በቀልብህ አትመለከትምን* (ألم تر) ልታውቅ ዘንዳ፡፡ ወደእነዚያ ወደአንተ በተወረደው ኪታብ እውነት ብለን ተቀብለናል ብለው የሚሞግቱትን ፥ ወደእነዚያ ካንተ በፊት በወረዱት መፅሃፍ አምነናል ብለው የሚሞግቱትን (አታይምን) ፥ በመካከላቸው በሚፈጠር አለመግባባት ወደጧጉት ሄደው መፋረድን ይፈልጋሉ፡፡ #አሏህ_ይህ_ማለቱ #ወደሚያልቁት እና በንግግሩም እውነት ብሏል ወደሚሉት ፥ ከአሏህ ሁክም ውጪ የእሱን ሁክም ወደሚወዱለት ጧጉት ሄደው ይፈረዳሉ፡፡ በእሱ እንዲክዱ ታዘው ነበር፡፡ እንደሚለው *አሏህ የሚፋረዱበትን ጧጉት ይዞላቸው በመጣው ነገር እንዲያስተባብሉ አዟቸው ነበር፡፡ የአሏህ ትዕዛዝ ተዉ፡፡ የሸይጧን ትዕዛዝ ተከተሉ፡፡ ሸይጧን ደግሞ ሩቅ የሆነ ጥመትን ሊያጠማቸው ይፈልጋል፡፡ ] 


📚ተፍሲር አጥጦበሪ


(قال أبو جعفر: يعني بذلك جل ثناؤه: " ألم تر "، يا محمد، بقلبك، فتعلم = إلى الذين يزعمون أنهم صدقوا بما أنـزل إليك من الكتاب، وإلى الذين يزعمون أنهم آمنوا بما أنـزل من قبلك من الكتب، يريدون أن يتحاكموا في خصومتهم إلى الطاغوت = #يعني إلى #من_يعظمونه_ويصدرون_عن_قوله_ويرضون_بحكمه_من_دون_حكم_الله =" وقد أمروا أن يكفروا به "، يقول: وقد أمرهم الله أن #يكذبوا بما جاءهم به الطاغوتُ الذي يتحاكمون إليه، فتركوا أمرَ الله واتبعوا أمر الشيطان =" ويريد الشيطان أن يضلهم ضلالا بعيدًا) 

፨ እነዚህ ሙናፊቆች የጧጉቱን ህግ የአሏህን ህግ ትተው እሱን ይወዱ ነበር፡፡ እውነተኛ ነው ይላሉ፡፡ ያልቁታልም፡፡ ከአሏህ ሁክም ውጪ በሆነ ሑክም ወዶ መቀበል ደግሞ ኩፍር ነው፡፡ ምክንያቱም ወይ ትክክለኛ ነው ብሎ ማመን ወይ ከአሏህ ሸሪዐ እኩል ማድረግ ፥ ወይ ከአሏህ ሁክም ማሥበለጥ አለ፡፡ 


፨ ይህ የሚያረጋግጥልን የአሽ-ሻጢቢ ንግግር እንመልከት..


يقول الشَّاطبي في الاعتصام : 

" *ወደ እነዚያ እነርሱ በአንተ ላይ በተወረደውና ከአንተ በፊትም በተወረደው አምነናል ወደሚሉት፤ አላየህምን በእርሱ እንዲክዱ በእርግጥ የታዘዙ ሲኾኑ ወደ ጣዖት መፋረድን ይፈልጋሉ፡፡* ልክ እዚጋ እነዚያ ሠዎች በተሃኩሙ አረጋግጠዋል፡፡ ግን መፋረዱ የነሡ ሥሜት በሚገጥም መልኩ እንዲሆን ፈለጉ፡፡ ይህም የሆነ ከሐቅ ስለጠመሙ ፥ ሁሉም ደግሞ መፋረጃ ነው (ልዩነት የለም) ማለታቸው ፥ ከዕብ ቢን አሽረፍ የሚፈርድበትን ወይም ሌሎቹ የሚፈርዱበትን ፥ ያው እንደረሡል ሠለሏሁ ዐለይሒ ወሠለም አምሳያ ነው ብለው ጠረጠሩ (አሰቡ)፡፡ ያላወቁት ነገር ቢኖር የረሡል ሠለሏሁ ዐለይሒ ወሠለም ሁክም ማለት የማይመለስ የሆነው የአሏህ ሁክም ነው፡፡ ከሱ ጋር የሌሎች በአሏህ ሁክም ላይ ካልገጠመ  ሑክሙ ውድቅ ነው (ተመላሽ ነው) ፡፡ ለዚህ አሏህ [ ሸይጧን ሩቅ የሆነ ጥመትን ሊያጠማቸው ይፈልጋል፡፡] ምክንያቱም አንቀፁ የሚጠቁመው *ኢስላም* ውስጥ በገቡ ሠዎች መውረዱን ነው፡፡ 


(وقال تعالى: {ألم تر إلى الذين يزعمون أنهم آمنوا بما أنزل إليك وما أنزل من قبلك يريدون أن يتحاكموا إلى الطاغوت} فكأن هؤلاء قد أقروا بالتحكيم، غير أنهم أرادوا أن يكون التحكيم على وفق أغراضهم زيغا عن الحق، #وظنا_منهم_أن_الجميع_حكم، #وأن_ما_يحكم به كعب بن الأشرف أو غيره #مثل_ما يحكم به النبي صلى الله عليه وسلم، #وجهلوا أن حكم النبي صلى الله عليه وسلم هو حكم الله الذي لا يرد، #وأن_حكم_غيره معه #مردود إن لم يكن جاريا على حكم الله، فلذلك قال تعالى: {ويريد الشيطان أن يضلهم ضلالا بعيدا}، لأن ظاهر الآية يدل على أنها نزلت فيمن دخل في الإسلام)

📚 ኢዕቲሷም ፥ አሽ-ሻጢቢ


፨ ይህ ግልፅ ንግግር ነው፡፡ እነዚያ ሙናፊቆች የአሏህ ሁክምና የሌላው ሁክም እኩኩል አድርገው ያስቧቸው ነበር፡፡ 


እስካሁን ባየነው *የአሏህን ሑክም መተው ብቻውን* ወይም ወደሌላ ሸሪዐ መፈረድ ከኢስላም የሚያስወጣ ወንጀል አይደለም፡፡ ከኢስላም የሚያስወጣ ኩፍር ለመሆኑ ሌሎች ቀሪና (ተዛማጅ የሆኑ) ነገሮች ይፈልጋል፡፡ ለምሳሌ *ሪዷ* ሌላን ሁክም መውደድ ፥ ወይ ከሸሪዐ ህግ ሌላ ሠው ሠራሽ ይሻላል ማለት ፥ ወይ እኩል ናቸው ማለት የመሣሠሉ ነገሮች ተጎራብቶት ከተገኘ ትልቁ ኩፍር ይሆናል፡፡ 

 

፨ አሏህ ወደ ቀጥተኛ መንገድ ይምራን፡፡ ወልሐምዱሊላሂ ረቢል ዐለሚን፡፡

Friday, November 29, 2019

☑️ * ዑዝር ቢል-ጀህልና የሙሂቡዲን ግልፅ ማደናገሪያዎች *

🔘ክፍል አንድ(3)

፨ በአሏህ ስም እጀምራለሁ፡፡ በረሱል ሰለሏሁ ወለይሒ ወሰለም ላይ ዘወትር የአሏህ እዝነት ይውረድ፡፡

-በዚህ ፅሁፍ በቀጥታ የአህሉ ሱናዎች አቋም እናረጋግጣለን፡፡ ሙኻሊፎች (ትክክለኛውን መንገድ) የሚቃረኑ ሰዎች ንግግር ደግሞ በስተመጨረሻ እንመለከተዋለን፡፡

[ ይህ (ሙስሊም ነኝ የሚለው)  ግለሰብ ኩፍር ወይም ሽርክ ላይ ከወደቀ ቀጥታ ከማክፈራችን በፊት የነገሩን ኩፍርነት እና ሽርክነት ሊብራራለት ይገባል።ከዚያ በኋላ ሽርኩ ላይ ከፀና ይከፍራል።] ይላል ሹብሃው፡፡

ይህ ባጢል አባባል ከቁርኣን የተለያዩ አስረጅ የሆነ አንቀጾች እያመጣን ውድቅ እናደርገዋለን፡፡

•ማሥረጃ(4) አሏህ እንዲህ ብሏል:

5፡103 " ከበሒራ ከሳኢባም ከወሲላም ከሓምም አላህ ምንንም (ሕግ) አላደረገም፡፡ ግን እነዚያ የካዱት በአላህ ላይ ውሸትን ይቀጣጥፋሉ፡፡ አብዛኞቻቸውም አያውቁም፡፡" ሱራ አልማኢዳ፡103
مَا جَعَلَ اللَّهُ مِنْ بَحِيرَةٍ وَلَا سَائِبَةٍ وَلَا وَصِيلَةٍ وَلَا حَامٍ وَلَكِنَّ الَّذِينَ كَفَرُوا يَفْتَرُونَ عَلَى اللَّهِ الْكَذِبَ وَأَكْثَرُهُمْ لَا يَعْقِلُونَ (103)

• ከዚህ አንቀፅ የምንረዳው አሏህ (ሱብሐነሁ ወተዐላ) እዚህ ሃራም ነገሮች ሰዎች ዲን አድርገው እንዲይዙ እንዳልደነገገ እየነገረን ነው፡፡ ነገር ግን እነዚያ #ካፊሮች ይህ ውሸት ወደ አሏህ በማሥጋት ይቀጥፋሉ፡፡ በዚህ የምንረዳው እነዚህ የዐረብ ሙሽሪኮች በሚሠሩት ኩፍርና ሽርክ መልዕክተኛ መጥቶ ሳያስጠነቅቃቸው ፥ ወይም ሽርክ ላይ እንደሆኑ ሳይብራራላቸው #ሙሽሪክ_ካፊር ተብለዋል፡፡

ሙሽሪክ ያስባላቸው በጅህልናቸው ምክንያት ሽርክ በመሥራታቸው እንጂ *ተዉ ሽርክ አትስሩ ሲባሉ እንቢ ሽርክ ይሻለናል* ብለው አይደለም፡፡ ምክንያቱም ረሱል (ሰለሏሁ ዐለይሒ ወሰለም) ከመላካቸውም በፊት ሙሽሪክ ተብለዋል፡፡

ምናልባት እነዚህ ሙስሊም ነኝ የሚሉት እኮ * ሸሃደተይን ይመሠክራሉ* ትለኝ ይሆናል፡፡ ግን እነዚያም ሙሽሪኮች *ሐጅ ያደርጉ ነበር* *በካዕባ ጠዋፍ ያደርጉ ነበር* *በጭንቅ ሰዐት አሏህ ብቻ ይጠሩ ነበር* ሆኖም እነዚህ መልካም ስራቸው ውድቅ የሆነ በስራቸው ላይ ሽርክ ስለቀላቀሉ ነው፡፡

•ዒባዳን ከአሏህ ውጪ ላሉ ግዑዝ ነገሮች ስላቀረቡ ነው፡፡ ልክ እንደዚሁ *ሸሐደተይን* የመሠከሩ ሰዎች ከሽርክ ሙሉ በሙሉ ካልጠሩ ይህ ቃል መመሥከራቸው ሙስሊም አያደርጋቸውም፡፡ ምናልባት * ጃሒል እኮ ናቸው * ካልክም እነዚያ በኢስላም ተፈጥረው ፥ አያቶቻቸውን በጭፍን ተከትለው ሽርክ የሰሩ ቁረይሾችም *ጃሒል* ነበሩ፡፡ ግን አሏህ *በጅህልናቸው* ነው ሽርክ የሰሩት ብሎ ሙስሊም ናቸው አላለም፡፡

•ማሥረጃ(5) አሏህ እንዲህ ብሏል:



2:89 « ከነሱም ጋር ያለውን (መጽሐፍ) አረጋጋጭ የኾነ መጽሐፍ ከአላህ ዘንድ በመጣላቸው ጊዜ (ከመምጣቱ) በፊት በነዚያ በካዱት ላይ ይረዱበት የነበሩ ሲኾኑ ያወቁት ነገር በመጣላቸው ጊዜ በርሱ ካዱ፡፡ የአላህም ርግማን በከሓዲዎች ላይ ይኹን፡፡»
وَلَمَّا جَاءَهُمْ كِتَابٌ مِنْ عِنْدِ اللَّهِ مُصَدِّقٌ لِمَا مَعَهُمْ وَكَانُوا مِنْ قَبْلُ يَسْتَفْتِحُونَ عَلَى الَّذِينَ كَفَرُوا فَلَمَّا جَاءَهُمْ مَا عَرَفُوا كَفَرُوا بِهِ فَلَعْنَةُ اللَّهِ عَلَى الْكَافِرِينَ (89)

፨ ይህ አንቀጽ የሚያስረዳን በአሏህ የሚያጋራ ሰው በየትኛውም ዘመንም ሆነ ፥ ቦታ ሙሽሪክ መሆኑ ነው፡፡ ምክንያቱም እነዚያ *ይረዱት የነበሩት* ( يَسْتَفْتِحُونَ) አይሁዶች ናቸው፡፡ በማን ከተባለ *በእነዚያ በካዱቱ* ( عَلَى الَّذِينَ كَفَرُوا) እነሱም የ "የስሪብ" ሰዎች ናቸው፡፡ አሏህ ግን ገና ረሱል (ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም) ሳይላኩ በፊት የነበሩ ፥ ሑጃ ያልደረሳሠቸው የ "የስሪብ" ሰዎች ካፊር መሆናቸው አረጋገጡ፡፡ እነዛ ሰዎች *አንድ ሰው ኩፍር ላይ መሆኑ ሳይነገረው ፥ ሽርኩ ሳይብራራለት አይከፍርም ይላሉ* ይኸው አሏህ ሽርክ ላይ መሆናቸው ያልተብራራቸው ሰዎች #ካፊር ብሎ ጠራቸው፡፡ *ላ ኢላሃ ኢለሏህ* የሚለው ቃል የሚጠቅመው ከሽርክ ለፀዳ ሰው ነው፡፡

እነዚህ ሰዎች የሚያስጠነቀቅ መልዕክተኛ ሳይመጣላቸው፥ በጅህልናቸው ሽርክ ላይ በመሆናቸው *ሙሽሪክ* ከተባሉ ፥ መልዕክተኛ ተልኮላቸው ፥ ቁርኣን ደርሷቸው ፥ በአሏህ የሚያጋሩ ሰዎች እንዴት *ሙስሊም* ይባላሉ? ፡፡

ኢንሻ አሏህ ሌሎችም ማሥረጃዎች ቀጥለው ይቀርባሉ፡፡

🔘ወቢላሒ አት-ተውፊቅ🔘

✍🏼አቡ ሙስሊም
☑️ @aqida_muwehid

Thursday, November 28, 2019

☑️ * ዑዝር ቢል-ጀህልና የሙሂቡዲን ግልፅ ማደናገሪያዎች *

🔘ክፍል አንድ(2)

፨ በአሏህ ስም እጀምራለሁ፡፡ በረሱል ሰለሏሁ ወለይሒ ወሰለም ላይ ዘወትር የአሏህ እዝነት ይውረድ፡፡

-በዚህ ፅሁፍ በቀጥታ የአህሉ ሱናዎች አቋም እናረጋግጣለን፡፡ ሙኻሊፎች (ትክክለኛውን መንገድ) የሚቃረኑ ሰዎች ንግግር ደግሞ በስተመጨረሻ እንመለከተዋለን፡፡

[ ይህ (ሙስሊም ነኝ የሚለው)  ግለሰብ ኩፍር ወይም ሽርክ ላይ ከወደቀ ቀጥታ ከማክፈራችን በፊት የነገሩን ኩፍርነት እና ሽርክነት ሊብራራለት ይገባል።ከዚያ በኋላ ሽርኩ ላይ ከፀና ይከፍራል።] ይላል ሹብሃው፡፡

ይህ ባጢል አባባል ከቁርኣን የተለያዩ አስረጅ የሆነ አንቀጾች እያመጣን ውድቅ እናደርገዋለን፡፡

•ማሥረጃ(1) አሏህ እንዲህ ብሏል:

12:103 «አብዛኛዎቹም ሰዎች (ለማመናቸው) ብትጓጓም የሚያምኑ አይደሉም፡፡»

12:104 «በእርሱም (በቁርአን) ላይ ምንም ዋጋ አትጠይቃቸውም፡፡ እርሱ ለዓለማት ግሳጼ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡»

12:105 «በሰማያትና በምድርም ካለችው ምልክት ብዙይቱ እነሱ ከርሷ ዘንጊዎች ኾነው በርሷ ላይ ያልፋሉ፡፡»

12:106 «አብዛኞቻቸውም፤ እነሱ አጋሪዎች (ሙሽሪኮች) ኾነው እንጂ በአላህ አያምኑም፡፡»

وَمَا أَكْثَرُ النَّاسِ وَلَوْ حَرَصْتَ بِمُؤْمِنِينَ (103) وَمَا تَسْأَلُهُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ إِنْ هُوَ إِلَّا ذِكْرٌ لِلْعَالَمِينَ (104) وَكَأَيِّنْ مِنْ آَيَةٍ فِي السَّمَوَاتِ وَالْأَرْضِ يَمُرُّونَ عَلَيْهَا وَهُمْ عَنْهَا مُعْرِضُونَ (105) وَمَا يُؤْمِنُ بِاللَّهِ إِلَّا وَهُمْ مُشْرِكُونَ.
•ይህ አንቀፅ የሚያስተላልፈው መልዕክት ምንድነው? ከዑዝር ቢል-ጀህል ጋር ምን አገናኘው?፡፡  ይህን የቁርኣን አንቀጽ የወረደበት ምክንያት አንዱ "ሙሽሪኮች" በካዕባ ላይ ጠዋፍ ያደርጉ ነበር፡፡ እዛም ተልቢያ ይሉ ነበር፡፡ ተልቢያውም * ለበይክ ላ ሸሪከ ለክ፡፡ ኢላ ሸሪከን ሁወ ተምሊኩሁ ወማ መለክ፡፡* ይሉ ነበር፡፡ (ሙስሊም እንደዘገበው)፡፡ ታድያ እነዚህ ሙሽሪኮች ከነበራቸው እምነት መካከል "ሰማይ ማን ነው የፈጠረው?" "ምድር ማን ፈጠረው?" ተብለው ሲጠየቁ *አሏህ ነው* ብለው ይመልሱ ነበር ከዚህ ጋር ግን ሙሽሪኮች ናቸው፡፡ በአሏህ ሩቡቢያ ቢያረጋግጡም ፥ ከርሱ ውጪ ያለ ነገር በማምለካቸው "ሙሽሪክ ሆኑ"፡፡ ይህን አንቀጽ የወረደው በመካ ነው፡፡

ረሱል ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም በመካ እያሉ የተውሂድ ዳዕዋ ሁሉም ቦታ አልተዳረሰም ነበር፡፡ ሆኖም ግን አሏህ በአብዛኞቹ ላይ ሙሽሪክ መሆናቸው ገለጸ፡፡ ይህ እንኳን እንደኛ ዘመን ያሉ ቁርኣንና ሀዲስ የደረሳቸው ሰዎች ይቅርና ሪሳላ ያልደረሳቸውም ሰዎች ቢሆኑ በአሏህ እስካጋሩ ድረስ ሙሽሪክ ይባላሉ፡፡

እንደሚባለው ከሆነ እነዚህ ሰዎች የሚሠሩት ስራ ሽርክና ኩፍር መሆኑ ሳይነገራቸው "ሙሽሪክ" አይባሉም ከተባለ ታድያ ለምን አሏህ ሙሽሪክ አላቸው? ረሱል (ሰዐወ) የረሱልነት ማዕረግ ሳይሰጣቸው በፊት ፥ ዳዕዋ ሳይጀምሩ በመካ ዙሪያ ጣዖታት የሚያመልኩ ሰዎች "ሙስሊም" ነበሩ? ሑጃ ስላልደረሳቸው፡፡ ይህ መጅኑን የሆነ ሰው እንጂ አይናገረውም፡፡

ምናልባት እነሱ እኮ መጀመርያ ወደ ኢስላም አልገቡም ትለኝ ይሆናል፡፡ እኔ የምልህ ደግሞ እነዚህ ሙሽሪኮች መጀመርያም ሙስሊም ነበሩ፡፡ የተፈጥሮ ሃይማኖታቸው እስልምና ነው፡፡ ግን የአባቶቻቸው መንገድ በጅህልና ተከትለው ነው ሙሽሪክ የሆኑት፡፡ ልክ እንደዛሬዎቹ፡፡ ስለዚህ ያለበት ስራ ሽርክ መሆኑ ተነግሮት የሚለው ሸርጥ ባጢል ነው፡፡

•ማሥረጃ(2)..አሏህ እንዲህ ብሏል

6:137 " እንደዚሁም ከ(ሙሽሪኮች) አጋሪዎቹ ለብዙዎቹ፤ ተጋሪዎቻቸው ሊያጠፉዋቸው ሃይማኖታቸውንም በእነሱ ላይ ሊያቀላቅሉባቸው (ሊያመሳስሉባቸው) ልጆቻቸውን መግደልን አሳመሩላቸው፡፡ አላህም በሻ ኖሮ ባልሠሩት ነበር፡፡ ከቅጥፈታቸውም ጋር ተዋቸው፡፡" አንዐም፡137
وَكَذَلِكَ زَيَّنَ لِكَثِيرٍ مِنَ الْمُشْرِكِينَ قَتْلَ أَوْلَادِهِمْ شُرَكَاؤُهُمْ لِيُرْدُوهُمْ وَلِيَلْبِسُوا عَلَيْهِمْ دِينَهُمْ وَلَوْ شَاءَ اللَّهُ مَا فَعَلُوهُ فَذَرْهُمْ وَمَا يَفْتَرُونَ.

•አሏህ በዚህ አንቀፅ እየነገረ ያለው እነዚያ ሙሽሪኮች ድህነትን ፈርተው ፥ ወይሌ " ልጆቻቸውን መግደል" "ሴት ልጆችን ከነ-ህይወታቸው መቅበር " የመሳሰለው አስቀያሚ ለብዙ ሙሽሪኮች መልካም ሆኖ ታያቸው ይላል፡፡ ይህን አስነዋሪ ስራ ይሰሩ የነበሩ ሰዎች በብዙ የተለያየ የአረቦች አካባቢ የነበሩ ናቸው፡፡ እንደ ማንኛውም ሰው በእስልምና ላይ ነው የተወለዱት ፥ ሆኖ ትክክለኛ የኢብራሒም ዲን ባለማወቃቸውና በአሏህ በማጋራታቸው "ሙሽሪክ" ሆኑ፡፡ አሏህም ቁርኣን ሳይመጣ በፊት ሙሽሪክ እንደነበሩ እየነገረን ነው፡፡ ስለዚህ አንድ ሰው በጅህልና ሽርክ ሰርቶ "ይህ ሽርክ መተው አለብህ" ተብሎ ባይነገረውም እንኳን ሙሽሪክ ይሆናል፡፡

፨ እነዚህ እኮ *ላ ኢላሃ ኢለሏህ* ይላሉ ትለኝ ይሆናል፡፡ ይህ *ላ ኢላሃ ኢለሏህ* የሚጠቅማቸው ከሽርክ ቢርቁ ነበር፡፡ ካልሆነማ በሽርክ ተጨማልቆ ላ ኢላሃ ኢሏህ ማለቱ ዋጋ የለውም፡፡

•ማሥረጃ(3)...አሏህ እንዲህ ብሏል፦

16:35 «እነዚያም (ጣዖታትን) ያጋሩት «አላህ በሻ ኖሮ ከእርሱ ሌላ እኛም አባቶቻችንም ምንንም ባልተገዛን ነበር፤ ያለእርሱም (ትእዛዝ) ምንንም እርም ባላደረግን ነበር አሉ፡፡» እነዚያም ከነሱ በፊት የነበሩት እነደዚሁ ሠሩ፡፡ በመልክተኞቹም ላይ ግልፅ ማድረስ ብቻ እንጂ ሌላ የለባቸውም፡፡»
وَقَالَ الَّذِينَ أَشْرَكُوا لَوْ شَاءَ اللَّهُ مَا عَبَدْنَا مِنْ دُونِهِ مِنْ شَيْءٍ نَحْنُ وَلَا آَبَاؤُنَا وَلَا حَرَّمْنَا مِنْ دُونِهِ مِنْ شَيْءٍ كَذَلِكَ فَعَلَ الَّذِينَ مِنْ قَبْلِهِمْ فَهَلْ عَلَى الرُّسُلِ إِلَّا الْبَلَاغُ الْمُبِينُ (35)

• እነዚህ ሰዎች ከዚህ ሽርክ ተከልከሉ ተብለው እምቢ ብለው አይደለም * ሙሽሪክ * የተባሉት፡፡ ነገርግን በጅህልናቸው ምክንያት አያቶቻቸውን ተከትለው ሽርክ በመሥራታቸው ነበር፡፡ ለጃሒልማ ዑዝር ቢኖረው ኖሮ እነዚህ *ሙስሊም* ይባሉ ነበር፡፡ ምክንያቱም ጃሂሎች ናቸው ተውሂድ አያውቁም፡፡ ግን ሑጃ ደርሷቸው እንቢ ባይሉም አሏህ "ሙሽሪክ አላቸው፡፡

• ዛሬ እነዚህ ሙስሊም ነን እያሉ በአሏህ የሚያጋሩት እኮ መልዕክተኛ ተላከላቸው ፥ ቁርኣን ደረሳቸው ፥ ሆኖም በአሏህ ያጋራሉ፡፡

፨ ስለዚህ [ ከማክፈራችን በፊት ስለ ሚሠራው ሽርክ ፥ ስለ ሚሠራው ኩፍር እናስረዳዋለን፡፡ አልመለስም ካለ እናከፍረዋለን፡፡ ] የተባለው አባባል ከነዚህ የቁርአን አንቀፆች ጋር የሚጣረስ ነው፡፡

ምክንያቱም እነዚህ አረቦች ምንም መልዕክተኛ ሳይላክላቸው ፥ የሚያስረዳቸው ዓሊም ሳይገኝ በሰሩት ሽርክ ሙሽሪክ ተብለዋልና፡፡ ኢንሻ አሏህ ይቀጥላል፡፡

🔘ወቢላሒ አት-ተውፊቅ🔘

✍🏼አቡ ሙስሊም
☑️ @aqida_muwehid
☑️ * ዑዝር ቢል-ጀህልና የሙሂቡዲን ግልፅ ማደናገሪያዎች *

🔘ክፍል አንድ(1)

፨ በአሏህ ስም እጀምራለሁ፡፡ በረሱል ሰለሏሁ ወለይሒ ወሰለም ላይ ዘወትር የአሏህ እዝነት ይውረድ፡፡

በመጀመርያ በአሏህ የሚያጋራ ሰው ጃሒል ከሆነ ሙሽሪክ እንለዋለን ወይስ ሙስሊም እንለዋለን?" የሚለው ነጥባችን ሲሆን በሙሂቡዲንና በአጠቃላይ "ሙርጂኣዎች" "ጀህምዮች" "አሽዓርዮች" መንሐጅ መሠረት *ሙስሊም* ይባላል፡፡ በሐቅ ላይ መንገዳቸው ባደረጉ ሙስሊሞች ዘንድ ደግሞ "ሽርክ የሚሠራ ሰው ጃሒል ቢሆንም ሙሽሪክ ነው የሚል ግልፅ አቋም አለ፡፡ *

ይህ በሰፊው አብራራለሁ፡፡ አሁን ሙሂቡዲን የጻፈው መሆኑን የተላከልኝ ፅሁፍ ከማሥረጃ አንጻር እንመዝነው፡፡
[....] 👈 የሙሂቡዲን ፅሁፎች የማሥቀምጥበት ምልክቴ ሲሆን (.....) 👈ለማብራርያ የምጠቀማቸው ገለፃዎች የማሥቀምጥበት ምልክት ነው፡፡

ወቢላሂ አትተውፊቅ !!

[ ማንኛውም ሙስሊም ነኝ ያለ እና በአሏህ ብቸኛ ተመላኪነት እንዲሁም በመልክተኛው(ሰ.ዐ.ወ) መልክተኝነት ያመነ ሁሉ ሙስሊም ነው። እስልምናው በእርግጠኝነት ፀድቆለታል። ] ይላል፡፡

✉መልስ፦ ይህ ንግግር ሐቅ ነው፡፡ እኛም በአሏህ ብቸኛ ተመላኪነት በ"አንደበቱ ፥ በቀልቡ ፥ በሰውነቱ" ያረጋገጠ ሰው ፥ እንዲሁ በረሱልﷺ መልዕክተኝነት በትክክል ያረጋገጠ ሰው *ሙስሊም* ነው ብለን እናምናለን፡፡ እስልምናውም በእርግጠኝነት ፀድቆለታል፡፡

[ይህ ግለሰብ ኩፍር ወይም ሽርክ ላይ ከወደቀ ቀጥታ ከማክፈራችን በፊት የነገሩን ኩፍርነት እና ሽርክነት ሊብራራለት ይገባል።ከዚያ በኋላ ሽርኩ ላይ ከፀና ይከፍራል።] ይላል፡፡

✉መልስ፦ እንግዲህ የመንገዳችን ልዩነት ከዚህ ይጀምራል፡፡ ይህ በአሏህና በመልዕክተኛው ﷺ አምኛለሁ ሲል የነበረው ሰው ይህ እምነቱ አፍርሶ በአሏህ ቢያሻርክና ከአሏህ ውጪ የሆነ ሌላ ህያውም ይሁን ግዑዝ ነገር ቢያመልክ "ሙሽሪክ" አይሆንም አሉ፡፡ እኛ ደግሞ ሙሽሪክ ይሆናል አልን፡፡ የነገሩ ሽርክነት ፥ ኩፍርነት ተነግሮት እምቢ ካለ እንጂ ሙሽሪክ አይሆንም አሉ፡፡ ይህ ባጢል ነው፡፡ ከቁርኣን ጋር በግልፅ የሚጋጭ እምነት ነው፡፡ እንዴት ከቁርኣን እንደሚጋጭ የሚከተሉት ማሥረጃዎች አስቀምጣለሁ፡፡ ከዚያ በፊት ሁለት ማጭበርበርያዎች ግልፅ መሆን አለባቸው፡፡ ሙሂቡዲንም ሆነ ሌሎችም ሙርጂኣዎች ስለተክፊር ሲነሳ ሁለት ሹብሃዎች ያቀርባሉ፡፡

1ኛው). የቀደምት ሙሽሪኮች ላይ የወረደ አንቀጽ ፥ እናንተ ወደ እስልምና የገባ ሰው ላይ ትጠቀማላቹህ፡፡ ይህ ቂያስ ደግሞ ውድቅ ነው አለ ሙሂቡዲን፡፡ ለምን ሲባል የሰጠው መልስ [ ልዩነት ከመኖር ጋር ቂያስ ውድቅ ነው፡፡  ያኛው ከመሠረቱ ካፊር ነው፡፡ ወደ ኢስላም አልገባም፡፡ ይህኛው ደግሞ ወደ ኢስላም ገባ አለ፡፡ ] ስለቂያስ የጠቀሰው ቃዒዳ ትክክል ቢሆን የተጠቀመበት ቦታ ግን ስህተት ነው፡፡  ከዚህ ንግግሩ የምንረዳው አሏህ ሰዎችን ሲፈጥራቸው ከመሠረቱ ሙሽሪክ ፥ ክርስቲያን ፥ አይሁድ  ፤ መጁስ አድርጎ ይፈጥራቸዋል የሚል መልዕክት ነው፡፡ ይህ ቁርኣንን ሃዲስን ውድቅ የሚያደርግ ባጢል ንግግር ነው፡፡ ምክንያቱም አሏህ ሁሉም የሰው ልጅ በእስልምና ላይ ነው የሚፈጥረው ፥ እንዲወለድ የሚያደርገው፡፡ ሰው ልጆች መሠረታቸው፥ አፈጣጠራቸው ተውሂድ ላይ መሆኑን፡፡ ይህ ቁርኣንና ሐዲስ የተረጋገጠ ሐቅ ነው፡፡ ሁሉ የቀደምት ሙሽሪክ ፥ ነሷራ ፥ አይሁድ ፥ መጁሲም ይሁን ሲፈጠር በትክክለኛ እስልምና ላይ ነው የሚፈጠረው፡፡ ማሥረጃችን አሏህ እንዲህ ብሏል፦

30:30 " ወደ እውነት ተዘንባይ ኾነህም ፊትህን ለሃይማኖት ቀጥ አድርግ፡፡ የአላህን ፍጥረት ያችን አላህ ሰዎችን በእርስዋ ላይ የፈጠረባትን (ሃይማኖት ያዟት)፡፡ የአላህን ፍጥረት መለወጥ የለም፡፡ ይህ ቀጥተኛ ሃይማኖት ነው፡፡ ግን አብዛኛዎቹ ሰዎች አያውቁም፡፡"
فَأَقِمْ وَجْهَكَ لِلدِّينِ حَنِيفًا فِطْرَةَ اللَّهِ الَّتِي فَطَرَ النَّاسَ عَلَيْهَا لَا تَبْدِيلَ لِخَلْقِ اللَّهِ ذَلِكَ الدِّينُ الْقَيِّمُ وَلَكِنَّ أَكْثَرَ النَّاسِ لَا يَعْلَمُونَ (30)
-ይህ የቁርኣን አንቀጽ ሲብራራ ( فَأَقِمْ وَجْهَكَ لِلدِّين ) የሚለው ዲንህን ለአሏህ ብቻ አጥራ ፥ ስራህም አስተካከክል ማለት ሲሆን (حَنِيفًا) የሚለው ደግሞ *ሙስተቂመን* ወይም *ቀጥ ያልክ ሆነህ የሚል ትርጉም አለው፡፡ ( فِطْرَةَ) የተባለውም "ዲን" ሲሆን እኛ የሰው ልጆች የተፈጠርንበት ኃይማኖት ማለት ነው፡፡ እሱም አሏህ ከአደም ጀርባ ሁሉም ሰዎች ላይ የያዘው ቃልኪዳኑ ሲሆን #ኢስላም ነው፡፡

-የአሏህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል ፦ " የሚወለድም ሰው በተፈጥሮው (ዲን) ላይ ሆኖ ይወለዳል፡፡ ወላጆቹም አይሁድ ፥ ነስራኒይ(ክርስቲያን) ፥ ወይም መጁስ(እሳት) አምላኪ ያደርጉታል፡፡"
" من يولد يولد على الفطرة ، فأبواه يهودانه أو ينصرانه أو يمجسانه.
• ከዚህ በግልፅ የምንረዳው ነገር ሰው ልጆች ሁሉ የጠመሙት የከፈሩት ሙስሊም ከነበሩ በኋላ ነው እንጂ ሙሽሪክ ሆኖ የሚወለድ የለም፡፡ እነ አቡ ጀህል ፥ እነ አቡ ለሃብ ሌልችም የቁረይሽ ሙሽሪኮች ሲወለዱ ሙስሊሞች ሆነው ተወልደው ነበር፡፡ ግን የአባቶቻቸው ፥ የአያቶቻቸው ሽርክ በጅህልናቸው ምክንያት ተክትለው ሰሩ፡፡ በዚህም ሙሽሪክ ሆኑ፡፡ ሙሽሪክ የሆኑት ሙርጂኣዎች እንደሚሉት *ተነግሯቸው እምቢ ሽርክ ይሻለናል* ብለው አይደለም፡፡ የረሱል ሰዐወ ዳዕዋ ሳይደርሳቸውም ሙሽሪክ ነበሩ፡፡ ዳዕዋ አልቀበልም ካሉ በኋላም የበለጠ ሙሽሪክ ሆነዋል፡፡

- በድሮ ሙሽሪኮችና አሁን ሙስሊም ነን ብለው ሽርክ በሚሠሩት መካከል ልዩነት አለ የተባለውም ባጢል ነው፡፡ ዝርዙር ቀጥለው ያንብቡ፡፡

1ኛው).  በመጀመርያ መታወቅ ያለበት ነገር አሏህ የሰው ልጆች ሁሉ በትክክለኛ ኃይማኖት ላይ ነው የፈጠራቸው፡፡ ቀጥ ባለው የተፈጥሮ ኃይማኖት እስልምና ላይ ነው የተፈጠርነው፡፡ በአለም የሚገኙ ነሷራዎች ፥ አይሁዶች ፥ መጁሶች (እሳት አምላኪዎች) ፥ ሙሽሪኮች ሁሉም ሙስሊም ሆነው ነው የተፈጠሩት የተወለዱት፡፡

በኋላም ቤተሰቦቹ ይህን ታዳጊ ህጻን አንዱ ነሷራ ያደርገዋል፡፡ አንዱ አይሁድ ያደርገዋል፡፡ አንዱ ልጁን መጁስ ያደርገዋል፡፡ የአሏህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል ፦
كل مولود يولد على الفطرة
"ሁሉም የሚወለደው በተፈጥሮ (እምነቱ) ላይ ነው፡፡" ብለዋል፡፡ አሏህም በቁርኣን የሰው ልጅ በትክክለኛ ዲን ላይ እንደፈጠረው ገልፇል፡፡ ሽርክ ወይም ኩፍር የሚንላቸው እስልምናን የሚያፈርሱ ነገሮች *ጧሪእ* ወይም ካለመኖር በኋላ የተገኙ ነገሮች ናቸው፡፡ እንጂ ከሰውዬው ጋር አብሮ የተፈጠሩ ነገሮች አይደሉም፡፡

-አል-ቃዲይ ኢብን አልዐረቢይ(543 ዓ.ሂ) እንዲህ ብሏል ፦ " አጠቃላይ ካፊሮች መሠረታቸው ሲታይ *ሙርተዶች* ናቸው፡፡ እነዚህ ኩፋሮች መጀመርያ ላይ "በተውሂድ" ላይ ነበሩ፡፡ አጥብቀውም ይዘውት ነበር፡፡ ከዚያም ከዚያም ተመለሱ፡፡ በዚህም ተገደሉ ፥ እንዲማረኩም ተደረጉ፡፡ " ይላል፡፡
📚ዐሪዶቱል አህወዚይ፡ 10/55

ስለዚህ ሙሥሊም ነኝ እያለ በአሏህ የሚያጋራውም ፥ ይህ በመሠረቱ ካፊር ያልነውም በመካከላቸው ልዩነት የለም፡፡ ሁለቱም በመጀመርያ የተፈጠሩበት እስልምና ትተው በጅህልናቸው ከአሏህ ውጭ ያለ ነገር ያመልካሉ፡፡

2ኛው). ከመጀመርያው ካፊር ነበር ያልነው ሰው ሽርክ ተግብሯል ፥ ልክ ራሱ ከሙሥሊሞች እየቆጠረ ያለው ሰውም *በአሏህ እንደሚያጋራው ሁሉ፡፡ ይህ ሁለቱም አንድ የሚያደርጋቸው ነገር ሲሆን የሚለያያቸው ነገር የለም፡፡ ያ ሙሥሊም ነኝ የሚለው ሰውዬ "ሶላት መሥገዱ" "ዘካ መሥጠቱ" ጾም መጾሞ" የመሳሰሉል ነገሮች ከሽርክ ጋር ግልጽ ማድረጉ ምንም ቦታ የሚሠጠው አይደሉም፡፡ ሽርክ ስራ ሁሉ ውድቅ ያደርጋልና፡፡ ያኛውም እኮ ጭንቀት በያዘው ጊዜ አሏህን ብቻ ነው የሚጠራው፡፡ ግን ከሽርክ ጋር በመሆኑ ዒባዳው ውድቅ ሆነ፡፡ አሏህ እንዲህ ብሏል ፦

31:32 " እንደ ጥላዎችም የሆነ ማዕበል በሸፈናቸው ጊዜ አላህን ሃይማኖትን ለእርሱ ብቻ ያጠሩ ሆነው ይጠሩታል፡፡ "
 (31) وَإِذَا غَشِيَهُمْ مَوْجٌ كَالظُّلَلِ دَعَوُا اللَّهَ مُخْلِصِينَ لَهُ الدِّينَ.
• እንደገናም ሙሽሪኮች በሌሎችም በሰላም ጊዜያቸውም ሐጅ ፥ ዑምራ የመሣሰሉ ነገሮች ይሰሩ ነበር፡፡ ግን ይህ የሚሠሩት በጣዖቶቻቸው ላይ እያጋሩ ነው፡፡ ሙስሊም ነኝ ብሎ ሽርክ ላይ የተዘፈቀውም እንደዚሁ ነው፡፡

3ኛው). በመሠረቱ ካፊሩ የምንለው (የጥንቱ ሙሽሪክ ) የሚሠራው ስራ ምን እንደሆነ ያውቅ ነበር፡፡ *ኢስቲጋሳው* *እርዱ* ያውቅ ነበር፡፡ ልክ እንደዚሁ ሙስሊም ነኝ እያለ የሚያጋራውም *ኢስቲጋሳው* *እርዱ* ሲፈፅም የስራው ምንነት ያውቃል፡፡ ሀለቱም ወደአሏህ ያቃርበናል ብለው ይሰሩታል፡፡ ይህ ሌላኛው አንድ የሚያደርጋቸው ነገር ነው፡፡

4ኛው). የጥንቱ ሙሽሪክ ሲሰራው የነበረው ሽርክ *የወሳኢጥ እና የተቀሩብ* ሽርክ ነው፡፡ ይህ ማለት በነሱ እና በአሏህ መካከል ጉዳያችን የሚያቃርቡልን ብለው የሚይዟቸው ተጋሪዎች ነበሩ፡፡

39:4 " እነዚያም ከእርሱ ሌላ (ጣዖታትን) ረዳቶች የያዙት «ወደ አላህ ማቃረብን እንዲያቀርቡን እንጅ ለሌላ አንገዛቸውም»
(ይላሉ)፡፡ "
وَٱلَّذِينَ ٱتَّخَذُوا۟ مِن دُونِهِۦٓ أَوْلِيَآءَ مَا نَعْبُدُهُمْ إِلَّا لِيُقَرِّبُونَآ إِلَى ٱللَّهِ زُلْفَى

• ልክ እንደዚሁ ሙስሊም ነኝ እያለ በአሏህ የሚያጋራውም ሼይኾቼ ፥ ወልዮቼ ፥ ነብያችን የተለያዩ ነገሮች ወደአሏህ ያቃርቡኛል ብሎ ያመልካል፡፡ ይህ ሌላኛ አንድ የሚያደርጋቸው ነገር ነው፡፡ ለዚህ ነው በሁክምም አንድ ናቸው የምንለው፡፡

5ኛው). ሁለቱም (የድሮው ሙሽሪክም ሆነ ሙስሊም ነኝ እያለ በአሏህ የሚያጋራው ) ሁለቱም ጃሒሎች ናቸው፡፡ አለማወቃቸው የማያውቁ ጃሂሎች ናቸው፡፡ ሁለቱም ባሉበት ሽርክ ላይ *እኛ ትክክለኛው መንገድ ላይ ነን* የሚሉ ናቸው፡፡ እነሱ ጠማማ ሆነው ሳለ፡፡ ይህም ሌላ ሁለቱም ሽርክ ሰሪዎች አንድ የሚያደርጋቸው ነው፡፡ በሁክም ላይም አንድ አይነት ሁክም እንድንሰጥ ያስገድደናል፡፡ አሏህ እንዲህ ብሏል ፦

7:30 " እነርሱ ሰይጣናትን ከአላህ ሌላ ረዳቶች አድርገው ይዘዋልና፡፡ እነርሱም (ቅኑን መንገድ) የተመራን ነን ብለው ያስባሉ፡፡"
إِنَّهُمُ اتَّخَذُوا الشَّيَاطِينَ أَوْلِيَاءَ مِنْ دُونِ اللَّهِ وَيَحْسَبُونَ أَنَّهُمْ مُهْتَدُونَ (30)
፨ሌላው የቁርኣን አንቀጾች ለድሮዎች የወረደው ላሁን ላሉት ማሥረጃ መጠቀም አይቻልም ለተባለው ይህን አንብቡ👇

•ነጥብ (1) :- የቁርአን አንቀፆች የሚያሰሰተላልፉት መልዕክት በወረዱበት ውስን ምክንያት ሳይሆን በሚያስተላልፉት ጥቅል መልዕክት ነው የሚታዩት፡፡

( العبرة بعموم اللفظ ليست بخصوص السبب )

• "ዋናው ነገር የቁርአን አንቀፆች በያዙት ጥቅል ንግግር እንጂ በተነገሩበት ውስን ምክንያት አይደለም የሚታዩት፡፡

فمن فعل فعل المُشركين تتناوله الآيات التي نزلت فيهم وينطبق عليه الوصف الذي وصفهم الله به .

• ሙሽሪኮች የሚሰሩትን ስራ የሰራ ሰው ፥ እነዚህ በሙሽሪኮች ላይ የወረዱ አንቀፆች ያገኙታል፡፡ እነሱን አሏህ የገለፃቸው ባህሪን በሱም ላይ ይረጋገጣል፡፡ ይህ በርካታ የዕውቀት ባለቤቶች የገለፁት ና ያስቀመጡት መርሆ ነው፡፡ ሽርክ ያው ሽርክ ነው፡፡ የሚሠራው ሰው ወይ ቦታ ወይም ዘመን ቢለያይም እንኳን፡፡

• ከዚህ የምንረዳው ነጥብ አሏህ በቁርአን የሚጠቅሳቸው አንቀፆች የሙሽሪኮችን ሁኔታና ፍርዳቸው ፥ በዛሬ ዘመን የነሱ ስራ የሚሠራ ነው በራሱ በቀጥታ ይመለከተዋል፡፡ እነዚያም ከአሏህ ውጪ ያለ ነገር ያመልኩ ነበር ፥ እነዚህም ከአሏህ ውጪ ያለን ነገር ያመልካሉ፡፡ እነዚያ ወደአሏህ ለመቃረብ ብለን ነው የሚል መከራከርያ ያመጣሉ እነዚህም አናመልካቸው ለመቃረብ ነው፡፡

• እንደው የዛሬዎቹ ከድሮዎቹ ሽርካቸውም የከፋ ነው፡፡ ልክ ሼይኹል ኢስላም ኢብን ዐብድልወህሃብ እንደገለፁት፡፡

قال شيخ الإسلام ابن تيمية رحمه الله فيمن جعل الآيات النازلة خاصة لمن نزلت بسببه ولا يشمل النوع أو المثال فقال

• ታላቁ ዐሊም ሼይኹል ኢስላም ኢብን ተይሚያህ (አሏህ ይዘንለት) እነዚህ የወረዱ አንቀፆች በነሱ ሰበብ ለወረደባቸው ሰዎች ብቻ የተወሰነ ነገር ስለሚያደርጉ ሰዎች ፥ ሌሎችን አካትትም ስለሚሉት እንዲህ ብሏል...

" አንድ ሙስሊም "ዚሃር"ን በተመለከተ የመጡ አንቀፆች ውስጥ አውስ ቢን አስሷሚት እንጂ ሌላ አይገባም ብሎ አይናገርም፡፡ የ"መራገም" አንቀፆችን ደግሞ ማንመሸ አያካትትም ዓሲም ቢን ዐዲይ እንጂ (ብሎ አንድ ሙስሊም አይናገርም) ፡፡ ኩፋሮችን የሚወቅሱ አንቀፆች የቁረይሽ ኩፋር እንጂ ሌላ አይገባም የመሳሰለው .. ይህ ሙስሊምም ሆነ አዕምሮ ያለው ሰው የሚናገረው ነገር አይደለም፡፡ "

[ መጅሙዕ አልፈታዋ ፡ 16/148]

: ( فلا يقول مسلم أن آية الظهار لم يدخل فيها إلا أوس بن الصامت وآية اللعان لم يدخل فيها إلا عاصم بن عدي وأن ذم الكفار لم يدخل فيه إلا كفار قريش ونحو ذلك مما لا يقوله مسلم ولا عاقل ) [الفتاوى 16/ 148].

• ኢማም አልሙጀዲድ አቡ ቡጠይን አን-ነጅዲይ (አሏህ ይዘንላቸው) እንዲህ ብሏል..

قال الإمام المجدد أبو بطين النجدي رحمه الله :
( أما قول من يقول أن الآيات التي نزلت بحكم المشركين الأولين فلا تتناول من فعل فعلهم فهذا كفر عظيم )

" ሙሽሪኮችን በተመለከተ የወረዱ አንቀፆች የነሱን ስራ የሰራ ሰው አያገኘውም የሚል ሰው ይህ ትልቅ የሆነ ኩፍር (ክህደት) ነው፡፡ "

، قال : ( ويلزم منه أن الحدود المذكورة في القرآن والسنة لأناس كانوا وانقرضوا ! فلا يُحد الزاني اليوم ولا تقطع يد السارق وبطل حكم القرآن ) [الدرر 10/418]

• እንዲህም ብለዋል ፦ " ይህ የሚያሲዘው በቁርአን ፥ በሃዲስ የተጠቀሱ ሓዶች (ቅጣቶች) ለነዚያ ድሮ ለጠፉት (ብቻ) ነበር ማለት ነው፡፡ ዚና የሰራ ሐድ አይቆምበትም፡ የሰረቀም እጁ አይቆረጥም፡፡ የቁርአን ሁክም ውድቅ ተደረገ ማለት ነው፡፡ "

[መጅሙዕ አልፈታዋ ፡ 10/418]

•ሼይኽ ሙሐመድ ሷሊህ አልዑሰይሚን እንዲህ ብሏል...
[ أن معنى قولنا العبرة بعموم اللفظ لا بخصوص السبب ] يعني أن الحكم لا يختص بعين الذي ورد من أحله ، وإنما يعم من كان مثل حاله. وقد نص على هذه القاعدة ابن دقيق العيد في شرح الحديث في العمدة وهو واضح.

📚 الكنز الثمين في تفسير ابن عثيمين :٥٤٤

" አልዒብራህ ቢዑሙሚ ለፍዚ ፥ ላ ቢኹሱሲ ሰበብ " የሚለው ንግግራችን ትርጉሙ ፦ ይህ ማለት አንድ ብይን (ሁክም) በዚያ በርሱ ምክንያት ለመጣበት ነገር ብቻ አይገደብም፡፡ ነገርግን የርሱን ሁኔታ የተመሳሰለ ሁሉ የሚያጠቃልል ነው፡፡ ይህን ቃዒዳ (መርሆ) በተመለከተ ኢብን ደቂቅ አልዒድ ዑምዳ ውስጥ ሐዲስ ሲያብራራ መረጃ አድርጎ ጠቅሶታል፡፡ እሱ ግልፅ ነገር ነው፡፡

[ አልከንዝ አስሰሚን ፊ ተፍሲር አልዑሰይሚን ፡ 544]

° ስለዚህ የቁርአን አንቀፆች የድሮ ሙሽሪክ ላይ የወረደ ነው ዛሬ ላሉት አይሆንም የሚለው ውድቅ የሆነ ሹብሃ ነው፡፡ የቀደምት ሙሽሪኮች ስራ የሰራ ሁሉ ያካትታል ፡፡

ሌሎች ማደናገርያዎቹ ትክክለኛውን መንገድ ካብራራን በኋላ እናያቸዋለን፡፡
🔘ወቢላሒ አትተውፊቅ🔘

✍🏼 አቡ ሙስለሊም
📱@Aqida_muwehid
☑️ abumuslim760.blogspot.com

የኢብኑ ተይሚያህ አቋም በተሃኩም ላይ...

  ፨ በአሏህ ሥም እጅግ በጣም አዛኝና በጣም ሩህሩህ በሆነው እጀምራለሁ፡፡ ፨ በዚህ ፅሁፍ ሼይኹል ኢሥላም ኢብኑ ተይሚያህን ከኸዋሪጆች አመለካከት እናጠራለን፡፡ አቡ ኢምራን ብዙዎች እንደምታውቁት ሁለት ገሪብ የኸዋሪጆችን...