፨ [ ሺዓ _ ምን ማለት ነው ? ]
..........................................................
- በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህና አዛኝ በሆነው እጀምራለሁ፡፡ ምስጋና ሁሉ ኃይማኖቱን ሙሉ አድርጎ ፥ ፀጋውን በኛ ላይ ለዋለልን አሏህ ይገባው፡፡ ከእርሱ በቀር በሐቅ የሚመለክ እንደሌለ እመሰክራለሁ፡፡ ለአለማት እዝነት ፥ ለጨለማው ብርሐን ተደርገው በተላኩት የአሏህ ነብይ "ሙሐመድ" ላይ የዘወትር የአሏህ በረከትና ረድኤት ይስፈን፡፡ በመቀጠል ፦
.......... ........... ........ ...... .....
በዚህ ፅሁፍና ተከታትለው በአሏህ ፍቃድ የሚቀርቡ ሌሎች አምዶች "ሺዓ" ተብለው የሚጠሩትንና ራሳቸውን ወደ ኢስላም የሚያስጠጉ ቡድኖች በተመለከት መጠነኛ ዳሰሳ ለማቅረብ ለመሞከር ነው፡፡ የዚህ አደገኛና ጠማማ ቡድን ምንነት በጥልቀት ለመፈተሽና ለማጥናት ጊዜንና አቅምን የሚጠይቅ እንደሆነ ግልፅ የሆነ ነገር ነው፡፡ ሆኖም በመሠረታዊነት ሊናውቃቸው የሚገቡና ሊታለፉ የማይገባቸው አንዳንድ ነጥቦች እንተዋወሳለን፡፡
.......... ........... .......... .......... .........
-መገጠምና እርዳታ ከአሏህ ብቻ እንከጅላለን፡፡ ለአንባቢያን ግልፅ እንዲሆን ዋቢ አድርጌ ከምጠቀምባቸው መፅሐፍት ቅርፅን ሙሉ በሙሉ ወስጄ ፥ የመልዕክት ይዘት ለማሳጠርና ዋና ዋና አንኳር ነጥቦች ለማቅረብ እሞክራለሁ፡፡
........ ........ ........ ........ .......... .....
- ስለ ቡድኑ(ሺዓ) ምንነት ከመግለፄ በፊት ፊርቃው የሚጠራበት ስያሜ የያዘው መልዕክት ማወቁ የሚበጅ ነው፡፡ አንዳንዴ በቁርአን ፥ በሐዲስ "ሺዓ" የሚለው ቃል ሊመጣ የሚችልበት አጋጣሚ ስላለ ለማወናበድ ውዥንብር ለመፍጠር በር ሊከፍት ይችላል፡፡ ስለዚህ ይህ ነጥብ መጀመርያ መቅረቡ ጥሩ ይሆናል፡፡ በዋናነት ለማጣቀሻነት ስለሺዓዎች ምንነት የሚያትተውን የዶ/ር ናስር አልቀፋሪይ መፅሐፍ በዋናነት ተጠቅሚያለሁ፡፡ መልካም ንባብ !!!
===========================
1). " ሺዓ በቋንቋ ያለው ትርጉም "
........ ........... ......... ......... .........
ኢብን ደሪይድ (321 ዓ.ሒ የሞተ ) እንዲህ ብሏል ፦
- فلان من شيعة فلان. أي ممن يرى رأيه.
(ፉላን ሚን "ሺዓቲ" ፉላን) ይባላል ፥ ይህ ማለት " የሱን አመለካከት የሚከተል ወይም በእገሌ ቡድን አመለካከት የሚሄድ ብሎ ለመግለፅ ነው፡፡
[ ጀምኸረቱ አልሉግጋ ፡ 3/63]
" እገል ከእገሌ ሺዓ(ጎራ) ነው ፡፡ " ያልነው፡፡ ስለዚህ በቀላሉ ይህ ቃል አንድ ጎራን ፣ቡድንን ለመግለፅ እንደሚፈለግበት ነው፡፡
° አል-አዝኸሪይ (አሏህ ይዘንለት) በ370 ዓ.ሒ የሞተ እንዲህ ብሏል ፦
- وشيعة أنصار الرجل وأتباعه ، وكل قوم اجتمعوا على أمرهم شيعة.
" ሺዓ የሚባለው ነገር ፦ የአንድ ሰው ረዳቶቹና ተከታዮቹ ማለት ነው፡፡ እያንዳንዱ ሰዎች በአንድ ያሰባሰባቸው ነገር "ሺዓ" እንለዋለን፡፡
[ ተህዚብ አልሉግጋ ፡ 3/61]
_ እንዲሁም ሺዓ የሚለው ቃል "ረዳት" እንዲሁም "በአመለካከት አንድ የሆነ ቡድን ፥ እንዲሁም በተመሳሳይ አመለካከት መሰባሰብ " የሚሉ ፍቺዎች ሊኖሩት እንደሚችል የቋንቋ ምሁራን ያስቀምጣሉ፡፡ በአንዳንድ ቦታዎች ይህን ቃል በቀጥታ " ታላቁ ሶሃቢይ ዓሊይ(ረ.ዐ) ና ቤተሰቦቹን ወዳጅ አድርገው የያዙ " በሚልም አንድምታ የተቀመጠበት ሁኔታ አለ፡፡ ነገሩ በአተኩሮት ለተመለከተው ሰው ግን በተለምዶ "ሺዓ" ተብለው የሚጠሩ ድንበር አላፊ ቡድኖች ለዓሊይም(ረ.ዓ) ሆነ ለቤተሰባቸው ረዳትና ተከታይ ሆነው አናገኛቸውም ፡፡ እንደውም ዓሊይ(ረ.ዓ) ና ቤተሰቦቹን የነበሩበት ቀጥተኛ ኃይማኖት ሲጥሱን በቢድዓና በሽርክ ድንበር ሲያልፉ ነው የምናገኛቸው፡፡
............ .............. .............. ........ .......
ሼይኹል-ኢስላም ኢብን ተይሚያህ (ረሒመሁሏህ) እንደሚናገረው ፦ ከዓሊይ (ረ.ዓ) የተዘገቡ በስምነት (8) አይነት ገላፃ የተናገራቸው ንግግሮች ይገኛሉ፡፡ ለምሳሌ በኩፋ ሚንበር ላይ ሆኖ " የዚህ ዑሜ ብልጫ ያለው ሰው ከነብዩ በኋላ አቡበክርና ዑመር (ረ.ዐ) ናቸው፡፡ አል-ቡኻሪይ የዘገበው፡፡
[ ሚንሐጅ አስሱናህ ፡ 4/137] እንዲሁም ከአንዳንዶች በተዘገበው ዓሊይ(ረ.ዓ) የማይከተል በእውነቱ (ሐቂቂይ) "ሺዒይ" እንደማይባሉ ጠቁመዋል፡፡ ምክንያቱም ከላይ እንዳሳለፍነው ፥ ሺዓ ሲባል በቋንቋውም የሚፈለግበት "ተከታይ" እንዲሁም "ረዳት" " በተመሳሳይ አቋም ላይ የሚገኝ" ለማለት ስለሆነ እነዚያ ደግሞ ለዚህ ነገር የገጠሙ ወይም የተገቡ አይደሉም፡፡
------------- ------------- -------------- ------ --- ------
" ሺዓ" የሚለው ቃል በቁርአን ውስጥ ያለው ትርጉም
................. ............ ......... ...........
ሺዓ ፦ የሚለው ቃል በቁርአን ውስጥ አስራ ሁለት ቦታ ላይ ተጠቅሶ ይገኛል፡፡ ኢብን አል-ጀውዚይ ፦ የተፍሲር ሊቃውንቶች " ሺዓ" የሚለው ቃል በአራት ቅርፅ እንዳስቀምጡት ይገልፃል፡፡ ( ይህ ማወቃቻን እነዚያ የጥመት ቡድኖች ስለኛ ነው አንቀፁ የሚያወራው ብለው እንዳያምታቱ ያግዘናል)፡፡
1). የመጀመርያው " ቡድን" በሚል ተጠቅሷል፡፡
إِنَّ ٱلَّذِينَ فَرَّقُوا۟ دِينَهُمْ وَكَانُوا۟ شِيَعًۭا
[ እነዚያ ሃይማኖታቸውን የለያዩ አሕዛብም የኾኑ በምንም ከእነሱ
አይደለህም፡፡ ]
[ وَلَقَدْ أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ فِى شِيَعِ ٱلْأَوَّلِينَ]
( ከአንተም በፊት በነበሩት በመጀመሪያዎቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልክተኞችን) በእርግጥ ልከናል፡፡ )
☞ በነዚህ አንቀፆች ሺዓ የሚለው ቃል "ቡድን" ወይም የሰዎች ስብስብ በሚያመለክት ሁኔታ ተቀምጧል፡፡
2). በሁለተኛ ፦ " ቤተሰብና የራስ ወገን (ዘርን) ለመግለፅ መጥቷል፡፡
وَدَخَلَ ٱلْمَدِينَةَ عَلَىٰ حِينِ غَفْلَةٍۢ مِّنْ أَهْلِهَا فَوَجَدَ فِيهَا رَجُلَيْنِ يَقْتَتِلَانِ هَٰذَا مِن شِيعَتِهِۦ وَهَٰذَا مِنْ عَدُوِّهِۦ ۖ فَٱسْتَغَٰثَهُ ٱلَّذِى مِن شِيعَتِهِۦ عَلَى ٱلَّذِى مِنْ عَدُوِّهِۦ
[ ከተማይቱንም ሰዎቿ በዝንጋቴ ጊዜ ላይ ሆነው ሳሉ ገባ፡፡ በእርሷም ውስጥ የሚጋደሉን ሁለት ሰዎችን አገኘ፡፡ ይህ ከወገኑ ነው፤ ይህም ከጠላቱ ነው፡፡ ]
☞ በዚህ አንቀፅ ሺዓ የሚለው ቃል "ወገን" ወይም "የራስ ዘር" የሚል አገባብ ነው የተፈለገበት፡፡ የበኒ እስራኤል ሰዎችን ነው የተፈለገበት፡፡
3). የመንገድ (የመዝሃብ) ባለቤቶችን ለመጥቀስ ቀርቧል፡፡
ثُمَّ لَنَنزِعَنَّ مِن كُلِّ شِيعَةٍ أَيُّهُمْ أَشَدُّ عَلَى ٱلرَّحْمَٰنِ عِتِيًّۭا
[ ከዚያም ከየጭፍሮቹ ሁሉ ከእነርሱ ያንን (እርሱ) በአልረሕማን ላይ በድፍረት በጣም ብርቱ የኾነውን እናወጣለን፡፡]
4). አራተኛ ፦ የተለያዩ ስሜት ባለቤቶችን ለመጠቆም ተጠቅሷል፡፡ አሏህ እንዲህ ብሏል ፦
قُلْ هُوَ ٱلْقَادِرُ عَلَىٰٓ أَن يَبْعَثَ عَلَيْكُمْ عَذ
َابًۭا مِّن فَوْقِكُمْ أَوْ مِن تَحْتِ أَرْجُلِكُمْ أَوْ يَلْبِسَكُمْ شِيَعًۭا وَيُذِيقَ بَعْضَكُم بَأْسَ بَعْضٍ ۗ ٱنظُرْ كَيْفَ نُصَرِّفُ ٱلْـَٔايَٰتِ لَعَلَّهُمْ يَفْقَهُونَ
«እርሱ (አላህ) ከበላያችሁ ወይም ከእግሮቻችሁ በታች ቅጣትን በእናንተ ላይ ሊልክ ወይም የተለያዩ ሕዝቦች ስትኾኑ ሊያደባልቃችሁና ከፊላችሁን የከፊሉን ጭካኔ ሊያቀምስ ቻይ ነው» በላቸው
............. .............. ............ ....... ......
- ኢብንል ቀይም (አሏህ ይዘንለት)
ስለዚህ ነጥብ ሲያመለክት እንዲህ ይላል ፦
" ምናልባት በዚህ ሁኔታ እንጂ በቁርአን አልመጣም ይሆናል፡፡ (ኢብን አልቀይም) ሲናገር ለዚህ ነገር ምክንያት ሲያስቀምጥ ይህ ነገር ያውቃል ፦ ሺዓ በሚለው ቃል አሽሺያዕ ስላለበት ነው፡፡ አል ኢሻዓህ የሚለው "መተሳሰር" "መሰባሰብ" የሚለውን ቃል የሚቃረን ነው፡፡ ለዚህም "ሺዓ" የሚለው ቃል በጠመመ ቡድን ላይ እንጂ አይነገርም፡፡ ስለተለያዩና ስለተበታተኑ፡፡
[ በዳኢዕ አልፈዋኢድ ፡ 1/155]
- ይህ "ሺዓ" የሚለው ቃል በአሏህ ኪታብ ውስጥያለው ትርጉም ይህ የምናውቀው ፊርቃ የሚመለከት እንዳልሆነ በነዚህ መረጃዎች ግልፅ ይሀሆናል፡፡
...... ....... ............. .............. ... ....... ......
ነገርግን እነዚህ የጥመት በድኖች የተለያየ የትርጉም ማንሻፈፍ በማድረግና አላዋቂዎች በማደናገር በቁርአን የተጠቀሰው "ሺዓ" የሚለው ቃል የነሱ መጤ አመለካከት ለመግለፅ የመጣ እንደሆነ አድርገው ማቅረብ ዳክረዋል፡፡ ቁርአን ከተገቢው የፍቺና የመልዕክት ይዘት አንጋደው ሠለፎች ሶሓቦች ዘንድ የማይታወቅን ተዕዊል በማስቀመጥ እያጣመሙ ይገልፁታል፡፡በነዚህ ሰዎች ኪታብ ውስጥ እንደተቀመጠው እንዲህ ብለዋ፦
۞ وَإِنَّ مِن شِيعَتِهِۦ لَإِبْرَٰهِيمَ
[ ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡ ]
- ሺዓዎችም በተፍሲራቸው እንዲህ ተርጉመውታል፡፡ '' ኢብራሂም ከዓሊይ 'ሺዓ' ነው፡፡ ማለት ነው አሉ፡፡ " ይህ ደግሞ የቁርአንን አገባብ የሚቃረን ነው፡፡ የኢስላም መሰረት የሚቃረን ነው፡፡ ይህ እንግዲህ ድንበር አላፊ ሺዓዎች እነዚያ አኢማዎቻቸውን ከነብያት የሚያስበልጡ የሆኑ ፥ የነሱ የተበላሸ ግንዛቤ ነው፡፡ ከአህለ ሱናህ በትክክል የተፈሰረው በዚህ አንቀፅ ከሠለፎችም የተገኘው ኢብራሒም (ዓ.ሰ) ከኑህ (ዓ.ሰ) ሺዓ ጋር ነበር ነው፡፡ በመንሐጁም በአካሔዱም ለማለት ነው፡፡ [ ተፍሲር አጥጦበሪይ ]
ከአንቀፁ ጋር የቃላት አገባብም ሆነ ትርጉም የሚገጥመው ይህ ነው፡፡ ምክንያቱም ቀድሞም በአንቀፁ ስለ ኑህ ዓ.ሰ ተጠቅሷልና፡፡
===========================
ይህ ርዕስ በዚህ ጀምረን ቀጣይ በሚቀርቡ ክፍሎች የበለጠ ስለጉዳዩ ግንዛቤ እንዲኖረን ለማድረግ በአሏህ ፍቃድ ጥረት ይደረጋል፡፡ አሏህ ለኸይር ሁሉ ይግጠመን፡፡
............. መልዕክቱን ለሌሎች በማስተላለፍ የራሳችን ድርሻ እንወጣ፡፡ ...................
© አቡ ሙስሊም ናሙስ
Saturday, December 15, 2018
□《የሺዓ ሐይማኖት 》□
■ ክፍል_2
ለአሏህ ሱብሐነሁ ወተዓላ ምስጋና ይገባው፡፡ በነብያችን ላይ የአሏህ ሶላትና ሰላም ይውረድ፡፡ በመቀጠል...
በመጀመርያው ክፍል ፦ ሺዓ የሚለው ቃል የሚሰጠው ትርጉምና ምንነቱ በተወሰነ መልኩ አይተን ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ከእምነቶቻቸው መካከል ጥቂቱን ለማስታወስ ያህል እናያለን፡፡
ሺዓ የቁርአን ሑጃነት (ማስረጃነት) በተመለከተ ምን ይላሉ ?? ይህ ክፍል በሶስት አይነት ከፍለን እናየዋለን፡፡
የመጀመርያው (1) ቁርአን በቀይም (ከአኢማዎቻቸው አንዱ) ካልሆነ በቀር ሑጃ (ማስረጃ) አይሆንም ማለታቸው፡፡
ሁለተኛ (2) የቁርአንን ዕውቀት መረዳት በአኢማዎቻቸው መገደባቸው፡፡
ሶስተኛው(3) የኢማማቸው ንግግር የቀርአን ጥቅል መልዕክትን #ይገድባል ፥ ልቅ የሆነውን ደግሞ በራሱ ገደብ ያስቀምጥለታል ማለታቸውን እናያለን፡፡
1▪የመጀመርያው ነጥብ ፦ ቁርሐን ሐጃ አይደለም ማለታቸው ነው፡፡ ይህ ነጥብ በበርካታ ሺዓዎች በሚመረኮዙባቸው መፅሐፎቻቸው የሚገልፁት እውነት እንደሆነ የተረጋገጠ ነው፡፡
አንድም ሰው " ቁርአን ሑጃ አይደለም" የሚል ቡድን ይኖራል ብሎ ጭራሽ አስቦ ላያውቅ ላይሆን ይችላል፡፡ ነገር ግን የአሏህ መልዕክተኛ ሰለለሏሁ አለይሒ ወሰለም እውነተኝነታቸው የሚገልፅ አንቀፅ የፈለገ አሏህ እንዲህ ብሏል ፦
أَوَلَمْ يَكْفِهِمْ أَنَّآ أَنزَلْنَا عَلَيْكَ ٱلْكِتَٰبَ يُتْلَىٰ عَلَيْهِمْ ۚ
[ እኛ መጽሐፉን በእነሱ ላይ የሚነበብ ኾኖ ባንተ ላይ ማውረዳችን አይበቃቸውምን? ] አንከቡት ፡51
ታላቁ መፅሐፍ ቁርአን መስካሪ ነው፡፡ ጠቋሚ መረጃ ነው፡፡ እንዲሁም ሑጃ አስረጅ ነው፡፡ ነገር ግን የሺዓ ሐይማኖት አስተማሪዎች ይህ #ሲቀቱል ኢስላም ብለው የሚጠሩት ( አል-ኩለይኒይ ) ኡሱል አልካፊ በተባለ ኪታቡ እነሱ ዘንድ ልክ አህለ ሱና ዘንድ አል-ቡኻሪይ እንደምንለው ነው የሚቆጥሩት፡፡ በዚህ ኪታቡ እንዲህ ዘግቧል ...
أن القرآن لا يكون حجة إلا بقيم ...وأن عليا كان قيم القرآن وكانت طاعته مفترضة ، وكان الحجة على الناس بعد الرسول. (أصول الكافي ١/١٨٨)
[ ቁርአን አስረጅ የሆነ ሑጃ አይሆንም በቀይም ቢሆን እንጂ፡፡ ዓሊይ ደግሞ የቁርአን ቀይም ነበር፡፡ እሱን መታዘዝም ግዴታ ነበር፡፡ በረሱል (ሰለሏሁ አለይሒ ወሰለም) በኋላ በሰዎች ላይ ሑጃ ነበር፡፡ ]
እንደዚህ አይነት ንግግሮቻቸው እነሱ ዘንድ በሚመረኮዙባቸው ኪታቦቻቸው ሰፍሮ ይገኛል፡፡ እንደ ሪጃል አልከሽፊይ ፥ ዒለል አልመሽራኢዕ ፥ አልመሐሲን ፥ ወሳኢል አሽሺዓ የመሳሰሉት ውስጥ ይገኛል፡፡
ይህ ንግግራቸው ይህ ዓቂዳቸው ምን ማለት ፈለሸገው ነው? ማለት የፈለጉት የቁርአን ጥቅሶችና መረጃዎች አሸንደ አስረጂነት ሊቀርቡ አይችሉም ወደ አኢማዎች ንግግር በመመለስ እንጂ ማለታቸው ነው??
ይህ ማለት ሑጃ ያለው በኢማም ንግግር እንጂ በአርራህማን ንግግር አይደለም ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት የኢማም ንግግር አሏህ በቁርአኑ ካብራራው የበለጠ ገርና ምርጥ አገላለፅ ነው እንደማለት ነው፡፡ ከዚህ ግልፅ ሆና የምናየው እነዚህ ሰዎች ሑጃ ያለው በኢማም ንግግር እንጂ በአሏህ አይደለም ብለው እንደሚያምኑ ነው፡፡ ለዚህ ነው ዝምተኛው ቁርአን ብለው የሰየሙት ፡ ኢማማቸውን ደግሞ ተናጋሪው ቁርአን፡፡ እንዲህም ይላሉ ፦
ዓሊይ እንዲህ ብሏል ፦
" ይህ የአሏህ መፅሐፍ ዝምተኛው ነው፡፡ እኔ ደግሞ ተናጋሪው የአሏህ መፅሐፍ ነው፡፡ "
📚 አልሐር አልዓሚሊይ ፡230
እንዲህ ብሏል ይላሉ ፦
" ያ ቁርአን አናግሩት ለናንተ አይናገርም፡፡ ስለሱ (እኔ) እነግራቹሐለሁ፡፡ "
📚ኡሱል አልካፊ ፡ 1/61
በሌላ ዘገባቸው ....
" ዓሊይ የአሏህ ኪታብ ተፍሲር ነው፡፡ " ይላሉ፡፡
📚 አልቢሐር ፡ 37/209
በተደጋጋሚም አኢማዎቻቸው ቁርአን ራሱ ናቸው ሲሉም ይሞግታሉ፡፡ ለዚህ እንዲህ የሚለው የአሏህ ቃል
واتبعوا النور الذي أنزل معه ....
-በዚህ አንቀፅ " ኑር " የተባለው ዓሊይና አኢማዎች ናቸው ብለው ይናገራሉ፡፡ ስለዚህ ከዚህ ተነስተን ምን ሊባል ነው አኢማዎች ከሰማይ ነው የተወረዱት ሊባል ነው፡፡
📚አልካፊ 1/194
- እንደገናም ቁርአን ለአንድ ሰው እሱም ለዓሊይ እንጂ ለማንም አልተፈሰረም ብለው ይሞግታሉ፡፡
[ ኡሱል አለሸካፊ ፡ 1/250 ]
ዓሊይ ራሱ ተፍሲር ቁርአን ነው ተብሎ ለምን ቀይሙል ቁርአን እንደሚሆን አናውቅም፡፡ ዓሊይ እሱ ራሱ ቁርአን ከሆነ ወይም በቁርአን ላይ ቀይም ከሆነ ለምንድነው ለሱ የሚፈሰርለት ወይም እንዴት እሱ ራሱ ተፍሲር ነው ተብሎ እንደገና ለሱ ይፈሰርለታል ? ይህ እርስ በራሱ የተማታ ንግግር ነው፡፡ ይህ አንዲ ኢስላምን ለማበላሸት ዚንዲቅ የቀጣጠፈው ኹራፋት እንደሆነ ግልፅ ነው፡፡ እንዴት እንዲህ ይባላል አሏህ ቁርአን ያወረደው የሰው ልጆች ሁሉ ሊመሩበት ነው፡፡ አሏህ እንዲህ ብሏል ፦
إِنَّ هَٰذَا ٱلْقُرْءَانَ يَهْدِى لِلَّتِى هِىَ أَقْوَمُ ً
[ ይህ ቁርኣን ወደዚያች እርሷ ቀጥተኛ ወደ ኾነችው መንገድ ይመራል፡፡ ] ኢስራእ 9
ታላቁ ቅኑ መንገድ የተመራው ኸሊፋው ዓሊይ (ረዲየሏሁ አንሁ) እንዲህ ብሏል ፦
" የአሏህ ኪታብ በውስጡ ከናንተ በፊት (ስለነበሩ ጉዳዮች) ዜና አለው፡፡ ከናንተ በሗላም ስለሚመጣው ዜና አለበት፡፡ በመካከላቹ ያለ ፍርድ ነው፡፡ እውነት ከውሸት የሚለይ እንጂ እንዲሁ ቀልድ አይደለም፡፡ የተወውም አሏህ ይቆርጠዋል፡፡ ከቁርአን ውጪ መመራት የፈለገ አሏህ ያጠመዋል፡፡ እሱ የአሏህ ጠንካራ ገመድ ነው፡፡ ጥበበኛ የሆነ አስታዋሽ ነው፡፡ ]
[ ፈዳኢል አልቁርአን ፡15 ; ቲርሚዚይ 290
ዐብድሏህ ቢን አባስ (ረዲየሏሁ አንሁ) እንዲህ ብሏል ፦
" ቁርአን ቀርቶና እንዲሁም ለሰራበት ሰው አሏህ በዱንያ ላያጠመው ፥ በአኼራ ከእድለቢሶች ላያደርገው ሐላፍትና ወስዶለታል፡፡ " ከዚያም ይህን አንቀፅ ቀራ....
فَمَنِ ٱتَّبَعَ هُدَاىَ فَلَا يَضِلُّ وَلَا يَشْقَىٰ
[ ከእኔም የኾነ መሪ ቢመጣላችሁ መሪየን የተከተለ አይሳሳትም አይቸገርምም፡፡ ]
የአሏህ ኪታብ ሑጃ ና መሪ በመሆኑ ላይ ብዙ አጨቃጫቂ ነገረሸ አይደለም፡፡ አብዛኛው ሙስሊም ያውቀዋል፡፡
ኢንሻ አሏህ በቀጣይ የቁርአን ሑጃነትና የሺዓዎች እረስ በራሳቸው የተጋጩ ንግግሮች እናያለን፡፡ ወሰላሙ አለይኩም፡፡
በቴሌግራም ለመከታተል....!!
↘↘↘↘↘↘↘↘↘↘↘
┏━ 🍃 ━━━━ 🍂 ━┓
✒️ @Aqida_muwehid🖋
┗━ 🍂 ━━━━ 🍃 ━┛
■ ክፍል_2
ለአሏህ ሱብሐነሁ ወተዓላ ምስጋና ይገባው፡፡ በነብያችን ላይ የአሏህ ሶላትና ሰላም ይውረድ፡፡ በመቀጠል...
በመጀመርያው ክፍል ፦ ሺዓ የሚለው ቃል የሚሰጠው ትርጉምና ምንነቱ በተወሰነ መልኩ አይተን ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ከእምነቶቻቸው መካከል ጥቂቱን ለማስታወስ ያህል እናያለን፡፡
ሺዓ የቁርአን ሑጃነት (ማስረጃነት) በተመለከተ ምን ይላሉ ?? ይህ ክፍል በሶስት አይነት ከፍለን እናየዋለን፡፡
የመጀመርያው (1) ቁርአን በቀይም (ከአኢማዎቻቸው አንዱ) ካልሆነ በቀር ሑጃ (ማስረጃ) አይሆንም ማለታቸው፡፡
ሁለተኛ (2) የቁርአንን ዕውቀት መረዳት በአኢማዎቻቸው መገደባቸው፡፡
ሶስተኛው(3) የኢማማቸው ንግግር የቀርአን ጥቅል መልዕክትን #ይገድባል ፥ ልቅ የሆነውን ደግሞ በራሱ ገደብ ያስቀምጥለታል ማለታቸውን እናያለን፡፡
1▪የመጀመርያው ነጥብ ፦ ቁርሐን ሐጃ አይደለም ማለታቸው ነው፡፡ ይህ ነጥብ በበርካታ ሺዓዎች በሚመረኮዙባቸው መፅሐፎቻቸው የሚገልፁት እውነት እንደሆነ የተረጋገጠ ነው፡፡
አንድም ሰው " ቁርአን ሑጃ አይደለም" የሚል ቡድን ይኖራል ብሎ ጭራሽ አስቦ ላያውቅ ላይሆን ይችላል፡፡ ነገር ግን የአሏህ መልዕክተኛ ሰለለሏሁ አለይሒ ወሰለም እውነተኝነታቸው የሚገልፅ አንቀፅ የፈለገ አሏህ እንዲህ ብሏል ፦
أَوَلَمْ يَكْفِهِمْ أَنَّآ أَنزَلْنَا عَلَيْكَ ٱلْكِتَٰبَ يُتْلَىٰ عَلَيْهِمْ ۚ
[ እኛ መጽሐፉን በእነሱ ላይ የሚነበብ ኾኖ ባንተ ላይ ማውረዳችን አይበቃቸውምን? ] አንከቡት ፡51
ታላቁ መፅሐፍ ቁርአን መስካሪ ነው፡፡ ጠቋሚ መረጃ ነው፡፡ እንዲሁም ሑጃ አስረጅ ነው፡፡ ነገር ግን የሺዓ ሐይማኖት አስተማሪዎች ይህ #ሲቀቱል ኢስላም ብለው የሚጠሩት ( አል-ኩለይኒይ ) ኡሱል አልካፊ በተባለ ኪታቡ እነሱ ዘንድ ልክ አህለ ሱና ዘንድ አል-ቡኻሪይ እንደምንለው ነው የሚቆጥሩት፡፡ በዚህ ኪታቡ እንዲህ ዘግቧል ...
أن القرآن لا يكون حجة إلا بقيم ...وأن عليا كان قيم القرآن وكانت طاعته مفترضة ، وكان الحجة على الناس بعد الرسول. (أصول الكافي ١/١٨٨)
[ ቁርአን አስረጅ የሆነ ሑጃ አይሆንም በቀይም ቢሆን እንጂ፡፡ ዓሊይ ደግሞ የቁርአን ቀይም ነበር፡፡ እሱን መታዘዝም ግዴታ ነበር፡፡ በረሱል (ሰለሏሁ አለይሒ ወሰለም) በኋላ በሰዎች ላይ ሑጃ ነበር፡፡ ]
እንደዚህ አይነት ንግግሮቻቸው እነሱ ዘንድ በሚመረኮዙባቸው ኪታቦቻቸው ሰፍሮ ይገኛል፡፡ እንደ ሪጃል አልከሽፊይ ፥ ዒለል አልመሽራኢዕ ፥ አልመሐሲን ፥ ወሳኢል አሽሺዓ የመሳሰሉት ውስጥ ይገኛል፡፡
ይህ ንግግራቸው ይህ ዓቂዳቸው ምን ማለት ፈለሸገው ነው? ማለት የፈለጉት የቁርአን ጥቅሶችና መረጃዎች አሸንደ አስረጂነት ሊቀርቡ አይችሉም ወደ አኢማዎች ንግግር በመመለስ እንጂ ማለታቸው ነው??
ይህ ማለት ሑጃ ያለው በኢማም ንግግር እንጂ በአርራህማን ንግግር አይደለም ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት የኢማም ንግግር አሏህ በቁርአኑ ካብራራው የበለጠ ገርና ምርጥ አገላለፅ ነው እንደማለት ነው፡፡ ከዚህ ግልፅ ሆና የምናየው እነዚህ ሰዎች ሑጃ ያለው በኢማም ንግግር እንጂ በአሏህ አይደለም ብለው እንደሚያምኑ ነው፡፡ ለዚህ ነው ዝምተኛው ቁርአን ብለው የሰየሙት ፡ ኢማማቸውን ደግሞ ተናጋሪው ቁርአን፡፡ እንዲህም ይላሉ ፦
ዓሊይ እንዲህ ብሏል ፦
" ይህ የአሏህ መፅሐፍ ዝምተኛው ነው፡፡ እኔ ደግሞ ተናጋሪው የአሏህ መፅሐፍ ነው፡፡ "
📚 አልሐር አልዓሚሊይ ፡230
እንዲህ ብሏል ይላሉ ፦
" ያ ቁርአን አናግሩት ለናንተ አይናገርም፡፡ ስለሱ (እኔ) እነግራቹሐለሁ፡፡ "
📚ኡሱል አልካፊ ፡ 1/61
በሌላ ዘገባቸው ....
" ዓሊይ የአሏህ ኪታብ ተፍሲር ነው፡፡ " ይላሉ፡፡
📚 አልቢሐር ፡ 37/209
በተደጋጋሚም አኢማዎቻቸው ቁርአን ራሱ ናቸው ሲሉም ይሞግታሉ፡፡ ለዚህ እንዲህ የሚለው የአሏህ ቃል
واتبعوا النور الذي أنزل معه ....
-በዚህ አንቀፅ " ኑር " የተባለው ዓሊይና አኢማዎች ናቸው ብለው ይናገራሉ፡፡ ስለዚህ ከዚህ ተነስተን ምን ሊባል ነው አኢማዎች ከሰማይ ነው የተወረዱት ሊባል ነው፡፡
📚አልካፊ 1/194
- እንደገናም ቁርአን ለአንድ ሰው እሱም ለዓሊይ እንጂ ለማንም አልተፈሰረም ብለው ይሞግታሉ፡፡
[ ኡሱል አለሸካፊ ፡ 1/250 ]
ዓሊይ ራሱ ተፍሲር ቁርአን ነው ተብሎ ለምን ቀይሙል ቁርአን እንደሚሆን አናውቅም፡፡ ዓሊይ እሱ ራሱ ቁርአን ከሆነ ወይም በቁርአን ላይ ቀይም ከሆነ ለምንድነው ለሱ የሚፈሰርለት ወይም እንዴት እሱ ራሱ ተፍሲር ነው ተብሎ እንደገና ለሱ ይፈሰርለታል ? ይህ እርስ በራሱ የተማታ ንግግር ነው፡፡ ይህ አንዲ ኢስላምን ለማበላሸት ዚንዲቅ የቀጣጠፈው ኹራፋት እንደሆነ ግልፅ ነው፡፡ እንዴት እንዲህ ይባላል አሏህ ቁርአን ያወረደው የሰው ልጆች ሁሉ ሊመሩበት ነው፡፡ አሏህ እንዲህ ብሏል ፦
إِنَّ هَٰذَا ٱلْقُرْءَانَ يَهْدِى لِلَّتِى هِىَ أَقْوَمُ ً
[ ይህ ቁርኣን ወደዚያች እርሷ ቀጥተኛ ወደ ኾነችው መንገድ ይመራል፡፡ ] ኢስራእ 9
ታላቁ ቅኑ መንገድ የተመራው ኸሊፋው ዓሊይ (ረዲየሏሁ አንሁ) እንዲህ ብሏል ፦
" የአሏህ ኪታብ በውስጡ ከናንተ በፊት (ስለነበሩ ጉዳዮች) ዜና አለው፡፡ ከናንተ በሗላም ስለሚመጣው ዜና አለበት፡፡ በመካከላቹ ያለ ፍርድ ነው፡፡ እውነት ከውሸት የሚለይ እንጂ እንዲሁ ቀልድ አይደለም፡፡ የተወውም አሏህ ይቆርጠዋል፡፡ ከቁርአን ውጪ መመራት የፈለገ አሏህ ያጠመዋል፡፡ እሱ የአሏህ ጠንካራ ገመድ ነው፡፡ ጥበበኛ የሆነ አስታዋሽ ነው፡፡ ]
[ ፈዳኢል አልቁርአን ፡15 ; ቲርሚዚይ 290
ዐብድሏህ ቢን አባስ (ረዲየሏሁ አንሁ) እንዲህ ብሏል ፦
" ቁርአን ቀርቶና እንዲሁም ለሰራበት ሰው አሏህ በዱንያ ላያጠመው ፥ በአኼራ ከእድለቢሶች ላያደርገው ሐላፍትና ወስዶለታል፡፡ " ከዚያም ይህን አንቀፅ ቀራ....
فَمَنِ ٱتَّبَعَ هُدَاىَ فَلَا يَضِلُّ وَلَا يَشْقَىٰ
[ ከእኔም የኾነ መሪ ቢመጣላችሁ መሪየን የተከተለ አይሳሳትም አይቸገርምም፡፡ ]
የአሏህ ኪታብ ሑጃ ና መሪ በመሆኑ ላይ ብዙ አጨቃጫቂ ነገረሸ አይደለም፡፡ አብዛኛው ሙስሊም ያውቀዋል፡፡
ኢንሻ አሏህ በቀጣይ የቁርአን ሑጃነትና የሺዓዎች እረስ በራሳቸው የተጋጩ ንግግሮች እናያለን፡፡ ወሰላሙ አለይኩም፡፡
በቴሌግራም ለመከታተል....!!
↘↘↘↘↘↘↘↘↘↘↘
┏━ 🍃 ━━━━ 🍂 ━┓
✒️ @Aqida_muwehid🖋
┗━ 🍂 ━━━━ 🍃 ━┛
🍃" የሺዓ ሐይማኖት " 🍃
______ ክፍል ሶስት (3) ______
ምስጋና ሁሉ ለብቸኛ ተመላኪው አሏህ ይድረስ፡፡ ሶላትና ሠላም በነብያችን ላይ ይውረድ፡፡
ይህ ካለፈው ትምህርት የቀጠለ አጠር ያለ ሺዓ ተብለው የሚጠሩና ራሳቸውን ወደ ኢስላም የሚያስጠጉ ቡድኖች ማንነት የምናይበት ነው፡፡
ሺዓዎች ከነብያችን በኋላ ሸሪዓ የሚደነግግ ፥ መዕሱም የሆኑ ( ከስህተት ጥቡቅ የሆኑ) ፥ ወንጀል የማይሰሩ ፥ ከአሏህ ወህይ የሚደርሳቸው ፥ ቁርአን የሚሽሩ ፥ ልቅ የሆነውን የሚገድቡ ፥ ጥቅል የሆነውን ለውስን የሚያደርጉ (የሚወሰሸኑ) የሆኑ 12 (አስራ ሁለት ) አኢማዎች አሉን ይላሉ፡፡
በነዚህ አኢማ ብለው በሚጠሯቸው ግለሰቦች የተነሳ ከፍተኛ ድንበር ማለፍ ላይ ወድቀው ሙሉ በሙሉ ጥመት ላይ ተዘፍቀው ይገኛል፡፡
፩). ሺዓዎች ለምንድነው የኢማማቸው ንግግር ቁርአን ይሽራል፡፡ ልቅ የሆነው ይገድባል ብለው የሚያምኑት ?
እነዚህ ቡድኖች " ኢማም " የሚሉትን ሰው የቁርአን ብቸው የግንዛቤ ባለቤት አድርገው እንደውም ኢማም ማለት " ተናጋሪ ቁርአን " ነው በማለት ይገልፃሉ፡፡ ኢማሞች የአሏህ ዒልም (እውቀት) ማከማቻና የወህይ ሚስጥር የሚጠብቀ ተደርገው ይታመናል፡፡
በነብያችን (ሰለሏሁ አለይሒ ወሰለም ) መሞት የአሏህ ዲን ኢስላም (ሸሪዓ መደንገግ) ሙሉ አልሆነም ብለውም ያምናሉ፡፡
እንደውም ያ የቀረው ያልተሟላው ሸሪዓ ለዓሊይ (ረዲየሏሁ አንሁ) ትተውለት ሔደዋል ብለውም ያምናሉ፡፡ ከዚያም ዓሊይ (ረ.ዐ) ከዚያች ከተሰጠው ነገር እያወጣ ዘመኑን የሚፈልገው አይነት ሸሪዓ ደነገገ ማለት ነው፡፡ አዑዙቢላህ ፡፡ ከዚያ የቀረው ሸሪዓ የማርቀቅ መብት ከሱ በኋላ ላሉት ተወላቸው፡፡
ሺዓዎች የአኢማዎቻቸውን ንግግር እንደ አሏህ ንግግር ነው የሚቆጥሩት፡፡ እንዲህ ይላሉ ፦
أن حديث كل واحد من الأئمة الطاهرين قول الله عز وجل ، ولا اختلاف في أقوالهم كما لا اختلاف في قوله تعالى.
📚 شرح جامع (على الكافي) : ٢/٢٧٢
" የጠሩ የሆኑ አአማዎቻችን እያንዳንዳቸው ንግግራቸው የአሏህ (ዐዘ ወጀል) ንግግር ነው፡፡ በንግግሮቻቸውም ምንም መጋጨት የለም፡፡ ልክ በአሏህ ንግግር ላይ መጋጨት የሚባል ነገር እንደሌለው ሁሉ፡፡ "
📚 ሸርህ አልጃሚዕ (በ አልካፊ) ፡ 2/272
እንደውም የአኢማዎች ንግግርም " ቃለ አሏህ " ( አሏህ እንዲህ ብሏል) ተብሎ ቢዘገብ ችግር የለውም ይላሉ፡፡ ለምሳሌ .....
ከአቡ ዐብድሏህ ( ጃዕፈር ኢብን ሙሐመድ አስሷዲቅ ማለታቸው ነው) ከሱ የተወራ ሐዲስ ከአባቱ ወይም ከአያቶቹ የሚዘግበው የሆነ የሰማ ሰው " አሏህ እንዲህ ብሏል " ብሎ ማውራት ይፈቀድለታል ይላሉ፡፡
📙 📚 ሸርህ አልጃሚዕ (በ አልካፊ) ፡ 2/272
በነሱ እምነት መሠረት ኢማማቸው ቁርአን በማንኛው ርዕስ ላይ የመወሰን የመገደብ ስልጣን አለው ብለው ያምናሉ፡፡ ወይም ቁርአን በቁርአን የመሻር መብት አለው ይላሉ፡፡
በዚህ ዘመን እንድ ትልቅ መሪያቸው የሚቆጥሩት ሰው እንዲህ ብሏል
" (ሸሪዓ መደንገግ) ቀስ በቀስ የሆነበት ጥበቡ ተጠናቋል፡፡ ሸሪዓዊ አህካሞችን ከፊሉ በማብራራት ሌላው ደግሞ በመደበቅ፡፡ ነገር ግን አሊይ (ረ.ዐ) በወስያዎቹ ላይ አስቀምጦታል፡፡ ሁሉ የተናዘዙለት ደግሞ ለሌላኛው ያስተላልፋል፡፡ ለጉዳዩ በሚገጥም ጊዜ ሊያሰራጨው፡፡ ...."
[ ሙሐመድ ሁሰይን አል ካሺፍ አልጊጣ አስሉ ሺዓ ፡ 77]
አኢማዎቻቸው ልክ እንደነብያቶች እንደመላኢኮች አድርገው ይቆጥሯቸዋል ፡፡ ከሰማይ የወረዱ አጠቃላይ የአሏህ ኪታቦች አኢማዎች ዘንድ አለ በማለት የሚቀጥፉ ናቸው፡፡
( ይህ በሚቀጥሉ ክፍሎች በመረጃ እናየዋለን፡፡ )
በቁርአን የተጠቀሱ አንዳንድ ለብዙ ነገር የሚያጠቃልሉ ቃላት በአኢማዎቻቸው አማክኝነት ያልተገደበውን ሲገድቡ ይስተዋላሉ፡፡ ለምሳል
ኩፍር ፥ ኩፋር ወይም ደግሞ ሽርክ ፥ ሙሽሪኮች ተብለው በአሏህ ኪታብ የተጠቀሱ ቃላት ኩፍር የሚለው ሁሉንም የክህደት አይነቶች የሚያጠቃል ሆኖ ሳለ ፥ ሽርክ ወይም ሙሽሪክ የሚለው ሁሉንም በአሏህ ማጋራትና በአሏህ ያጋራ ሰው የሚያጠቃልል ሆኖ ሳለ እነሱ ግን ለአላማቸው በሚያመች መልኩ ብቻ ይገድቡታል፡፡
በብዙ ዘገባዎቻቸው እንደተገኘው ኩፍር (ክህደት) የሚሉ ቃላት በ ዓሊይ (ረ.ዐ) ዊላያነት የካደ በሚል ይፈስሩታል፡፡ ሽርክ የሚለው ደግሞ ከአማማቸው ጋር ሌላ ኢማም መያዝ አድርገው ገድበውታል፡፡
- በአሏህ ኪታብ በጥቅሉ የተነገረ ነገር እነሱ ያለ መረጃ ይገድቡታል ፡፡ የኢማምያ ነጥብ ከኩፍርና ከሽርክ የበለጠ ነጥብ አድርገው ያምናሉ፡፡ ይህ የዓቅልም የነቅል የሚደግፈው ነገር አይደለም፡፡ በዚህ ከሙስሊሞች የጋራ ስምምነት ወጡ ፡፡
አሏህ እንዲህ ብሏል ፦
إِنَّآ أَنزَلْنَٰهُ قُرْءَٰنًا عَرَبِيًّۭا لَّعَلَّكُمْ تَعْقِلُونَ
( እኛ (ፍቹን) ታውቁ ዘንድ ዐረብኛ ቁርኣን ሲሆን በእርግጥ አወረድነው፡፡ )
በቀጣይ ከዚህ ጥመታቸው ከፊሎቹን ለማስታወስ ያህል እንጠቅሳለን፡፡
☞ ወቢላሒ አት-ተውፊቅ
📮 © አቡ ሙስሊም ናሙስ
📮ረጀብ 26 / 1439 ዓ.ሒ
አልኢንቲሳር ሊ'ሒዝቢላህ አልሙወሒዲን
telegram.me/aqida_muwehif
______ ክፍል ሶስት (3) ______
ምስጋና ሁሉ ለብቸኛ ተመላኪው አሏህ ይድረስ፡፡ ሶላትና ሠላም በነብያችን ላይ ይውረድ፡፡
ይህ ካለፈው ትምህርት የቀጠለ አጠር ያለ ሺዓ ተብለው የሚጠሩና ራሳቸውን ወደ ኢስላም የሚያስጠጉ ቡድኖች ማንነት የምናይበት ነው፡፡
ሺዓዎች ከነብያችን በኋላ ሸሪዓ የሚደነግግ ፥ መዕሱም የሆኑ ( ከስህተት ጥቡቅ የሆኑ) ፥ ወንጀል የማይሰሩ ፥ ከአሏህ ወህይ የሚደርሳቸው ፥ ቁርአን የሚሽሩ ፥ ልቅ የሆነውን የሚገድቡ ፥ ጥቅል የሆነውን ለውስን የሚያደርጉ (የሚወሰሸኑ) የሆኑ 12 (አስራ ሁለት ) አኢማዎች አሉን ይላሉ፡፡
በነዚህ አኢማ ብለው በሚጠሯቸው ግለሰቦች የተነሳ ከፍተኛ ድንበር ማለፍ ላይ ወድቀው ሙሉ በሙሉ ጥመት ላይ ተዘፍቀው ይገኛል፡፡
፩). ሺዓዎች ለምንድነው የኢማማቸው ንግግር ቁርአን ይሽራል፡፡ ልቅ የሆነው ይገድባል ብለው የሚያምኑት ?
እነዚህ ቡድኖች " ኢማም " የሚሉትን ሰው የቁርአን ብቸው የግንዛቤ ባለቤት አድርገው እንደውም ኢማም ማለት " ተናጋሪ ቁርአን " ነው በማለት ይገልፃሉ፡፡ ኢማሞች የአሏህ ዒልም (እውቀት) ማከማቻና የወህይ ሚስጥር የሚጠብቀ ተደርገው ይታመናል፡፡
በነብያችን (ሰለሏሁ አለይሒ ወሰለም ) መሞት የአሏህ ዲን ኢስላም (ሸሪዓ መደንገግ) ሙሉ አልሆነም ብለውም ያምናሉ፡፡
እንደውም ያ የቀረው ያልተሟላው ሸሪዓ ለዓሊይ (ረዲየሏሁ አንሁ) ትተውለት ሔደዋል ብለውም ያምናሉ፡፡ ከዚያም ዓሊይ (ረ.ዐ) ከዚያች ከተሰጠው ነገር እያወጣ ዘመኑን የሚፈልገው አይነት ሸሪዓ ደነገገ ማለት ነው፡፡ አዑዙቢላህ ፡፡ ከዚያ የቀረው ሸሪዓ የማርቀቅ መብት ከሱ በኋላ ላሉት ተወላቸው፡፡
ሺዓዎች የአኢማዎቻቸውን ንግግር እንደ አሏህ ንግግር ነው የሚቆጥሩት፡፡ እንዲህ ይላሉ ፦
أن حديث كل واحد من الأئمة الطاهرين قول الله عز وجل ، ولا اختلاف في أقوالهم كما لا اختلاف في قوله تعالى.
📚 شرح جامع (على الكافي) : ٢/٢٧٢
" የጠሩ የሆኑ አአማዎቻችን እያንዳንዳቸው ንግግራቸው የአሏህ (ዐዘ ወጀል) ንግግር ነው፡፡ በንግግሮቻቸውም ምንም መጋጨት የለም፡፡ ልክ በአሏህ ንግግር ላይ መጋጨት የሚባል ነገር እንደሌለው ሁሉ፡፡ "
📚 ሸርህ አልጃሚዕ (በ አልካፊ) ፡ 2/272
እንደውም የአኢማዎች ንግግርም " ቃለ አሏህ " ( አሏህ እንዲህ ብሏል) ተብሎ ቢዘገብ ችግር የለውም ይላሉ፡፡ ለምሳሌ .....
ከአቡ ዐብድሏህ ( ጃዕፈር ኢብን ሙሐመድ አስሷዲቅ ማለታቸው ነው) ከሱ የተወራ ሐዲስ ከአባቱ ወይም ከአያቶቹ የሚዘግበው የሆነ የሰማ ሰው " አሏህ እንዲህ ብሏል " ብሎ ማውራት ይፈቀድለታል ይላሉ፡፡
📙 📚 ሸርህ አልጃሚዕ (በ አልካፊ) ፡ 2/272
በነሱ እምነት መሠረት ኢማማቸው ቁርአን በማንኛው ርዕስ ላይ የመወሰን የመገደብ ስልጣን አለው ብለው ያምናሉ፡፡ ወይም ቁርአን በቁርአን የመሻር መብት አለው ይላሉ፡፡
በዚህ ዘመን እንድ ትልቅ መሪያቸው የሚቆጥሩት ሰው እንዲህ ብሏል
" (ሸሪዓ መደንገግ) ቀስ በቀስ የሆነበት ጥበቡ ተጠናቋል፡፡ ሸሪዓዊ አህካሞችን ከፊሉ በማብራራት ሌላው ደግሞ በመደበቅ፡፡ ነገር ግን አሊይ (ረ.ዐ) በወስያዎቹ ላይ አስቀምጦታል፡፡ ሁሉ የተናዘዙለት ደግሞ ለሌላኛው ያስተላልፋል፡፡ ለጉዳዩ በሚገጥም ጊዜ ሊያሰራጨው፡፡ ...."
[ ሙሐመድ ሁሰይን አል ካሺፍ አልጊጣ አስሉ ሺዓ ፡ 77]
አኢማዎቻቸው ልክ እንደነብያቶች እንደመላኢኮች አድርገው ይቆጥሯቸዋል ፡፡ ከሰማይ የወረዱ አጠቃላይ የአሏህ ኪታቦች አኢማዎች ዘንድ አለ በማለት የሚቀጥፉ ናቸው፡፡
( ይህ በሚቀጥሉ ክፍሎች በመረጃ እናየዋለን፡፡ )
በቁርአን የተጠቀሱ አንዳንድ ለብዙ ነገር የሚያጠቃልሉ ቃላት በአኢማዎቻቸው አማክኝነት ያልተገደበውን ሲገድቡ ይስተዋላሉ፡፡ ለምሳል
ኩፍር ፥ ኩፋር ወይም ደግሞ ሽርክ ፥ ሙሽሪኮች ተብለው በአሏህ ኪታብ የተጠቀሱ ቃላት ኩፍር የሚለው ሁሉንም የክህደት አይነቶች የሚያጠቃል ሆኖ ሳለ ፥ ሽርክ ወይም ሙሽሪክ የሚለው ሁሉንም በአሏህ ማጋራትና በአሏህ ያጋራ ሰው የሚያጠቃልል ሆኖ ሳለ እነሱ ግን ለአላማቸው በሚያመች መልኩ ብቻ ይገድቡታል፡፡
በብዙ ዘገባዎቻቸው እንደተገኘው ኩፍር (ክህደት) የሚሉ ቃላት በ ዓሊይ (ረ.ዐ) ዊላያነት የካደ በሚል ይፈስሩታል፡፡ ሽርክ የሚለው ደግሞ ከአማማቸው ጋር ሌላ ኢማም መያዝ አድርገው ገድበውታል፡፡
- በአሏህ ኪታብ በጥቅሉ የተነገረ ነገር እነሱ ያለ መረጃ ይገድቡታል ፡፡ የኢማምያ ነጥብ ከኩፍርና ከሽርክ የበለጠ ነጥብ አድርገው ያምናሉ፡፡ ይህ የዓቅልም የነቅል የሚደግፈው ነገር አይደለም፡፡ በዚህ ከሙስሊሞች የጋራ ስምምነት ወጡ ፡፡
አሏህ እንዲህ ብሏል ፦
إِنَّآ أَنزَلْنَٰهُ قُرْءَٰنًا عَرَبِيًّۭا لَّعَلَّكُمْ تَعْقِلُونَ
( እኛ (ፍቹን) ታውቁ ዘንድ ዐረብኛ ቁርኣን ሲሆን በእርግጥ አወረድነው፡፡ )
በቀጣይ ከዚህ ጥመታቸው ከፊሎቹን ለማስታወስ ያህል እንጠቅሳለን፡፡
☞ ወቢላሒ አት-ተውፊቅ
📮 © አቡ ሙስሊም ናሙስ
📮ረጀብ 26 / 1439 ዓ.ሒ
አልኢንቲሳር ሊ'ሒዝቢላህ አልሙወሒዲን
telegram.me/aqida_muwehif
Subscribe to:
Posts (Atom)
የኢብኑ ተይሚያህ አቋም በተሃኩም ላይ...
፨ በአሏህ ሥም እጅግ በጣም አዛኝና በጣም ሩህሩህ በሆነው እጀምራለሁ፡፡ ፨ በዚህ ፅሁፍ ሼይኹል ኢሥላም ኢብኑ ተይሚያህን ከኸዋሪጆች አመለካከት እናጠራለን፡፡ አቡ ኢምራን ብዙዎች እንደምታውቁት ሁለት ገሪብ የኸዋሪጆችን...
-
🔖 በአሏህ ሥም እጅግ በጣም ሩህሩህና እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው እጀምራለሁ፡፡ በዚህ ሁፍ በአሏህ እርዳታ በመታገዝ ወደ ጧጉት መፋረድ ምን እንደሆነ እና ወደ ጧጉትም መፋረድ ያለው ሁክም እንመለከታለን፡፡ በምን አይነት...
-
✔ በአሏህ ስም እጅግ በጣም አዛኝና ሩህሩህ በሆነው እጀምራለሁ፡፡ الحمد لله وصلاة وسلام على رسول الله وعلى آله وصحبه ومن والاه ..... أما بعد ° በዚህ አጠር ያለ ትምህርት ...
-
📌 [ አል-መድኸሉ ኢላ አልጃሚዕ ፊ ኩትቢ አል ኢማን ወርረድ ዓለል ሙርጂአህ ] -------------- ክፍል _ 2 -------------- بسم الله الحمد لله والصلاة والسلام على رسول ...