Tuesday, April 23, 2019

✿ ዑዝር ቢል-ጀህልና ማደናገርያዎች መግለጥ❀ (ክፍል-3)

[ በአላህ ስም እጅግ በጣም አዛኝ በጣም ሩህሩህ በሆነው]

፨ ምሉዕ የሆነ ምስጋና ለአለማቱ ጋታ ለአሏህ ይገባው፡፡ ሰላምና ደህንነት እንዲሁም ረድኤት ዘወትር በነብያች ሰለሏሁ ዐለይሒ ወሰለም ላይ ይውረድ፡፡

፨ቅርብ ጊዜ በአንድ የፌስቡክ ባልደረባችን የተፃፈ {በኢስላም ዑዝር ቢልጀህል ስለመኖሩ ግራ ለተጋባችሁ!} የሚል ተከታታይ ፅሁፍ አንብበን ነበር፡፡ የዚህ ፅሁፍ ጸሐፊ ባቀረበው ት/ቱ ቁርኣንና ሐዲስ እንዲሁም የሙስሊሞች የጋራ ስምምነት የሚጥስና የሚቃረን ሐሳብ አቅርቧል ብዬ አምናለሁ፡፡

ሆኖም ብዙዎች ይህ ስህተት ተመልከተው ሊያርሙት ስላልሞከሩ ወይም ስላልደረሳቸው ፥ በርካታ ሰዎች ይህን ፅሁፍ እንደማሥረጃ ከቦታ ወደቦታ ሲያስተላልፉ በማየቴ የማወቀውን ያህል የዑለሞች አስተምህሮት በማብራራት ሐቁን ለማስቀመጥ ሙከራ አድርጊያለሁ፡፡ አሏህ ሱብሐነሁ ወተዐላ ለሐቁ እንዲገጥመኝ እለምነዋለሁ፡፡

[ ፀሐፊው እንዲህ ይላል☞ ኢንሻ አላህ በኢስላም ዑዝር ቢልጀህል እዳለ ቁራኣናዊ ሀዲሳዊ እንድሁም የኡለሞችን ንግግር በተከታታይ ፅሁፍ ለማቅረብ እሞክራለሁ! ] የዚህ ፀሐፊ ስህተት ከዚህ ይጀምራል፡፡ ዑዝር ቢልጀህል ከሰዎች ሁኔታ ፥ ከአካባቢ ሁኔታ ፥ ከዘመን ሁኔታ ፥ የመሣሠሉት ጋር ቁርኝት ያለው ነጥብ በመሆኑ በልቁ "ዑዝር ቢልጀህል እንዳለ.." ብሎ መቅረብ አይገባውም ነበር፡፡ ምክንያቱም በቁርኣንም በሐዲስም በልቁ በጀህል ዐቃቤ ምክንያት(ዑዝር ቢልጀህል) አለ ተብሎ አልተነገረንም፡፡

 [ ፀሐፊው እንዲህ ይላል ☞ ዑዝር ቢልጀህል እንደሌሎች ኢጅቲሃድን እንደሚያስተናግዱ ርእሶች ነው። እንጅ #ከዐቂዳ ርእስ አይደለም!! ]
ይህ ንግግር የተጠቀሰበት ምክንያት ዑዝር ቢልጀህል መስጠት ፥ አለመስጠት ኺላፍ ያለበት ርዕስ ስለሆነ ከፊል ፥ ከፊሉን ማውገዝ የለበትም የሚል ድፍን ቃዒዳ ለማርቀቅ የተሞከረበት ነው፡፡

• እንጂ ባለማወቅ ሽርክ ላይ የወደቀ ሰው ሙሽሪክ ካፊር በመሆኑ ላይ ምንም ኺላፍ የለም፡፡ ቁርኣን ፥ ሐዲስ ፥ ኢጅማዕ ይህን ይመሠክራሉ፡፡ እሱ ግን ኺላፍ አለ ብሎ ለማስቀመጥ የሞከረው የተወሰኑ የሱን አካሔድ የሚደግፉለት ዐሊሞች ስም ጠቀሰና በሽርክ ዑዝር ቢልጀህል መስጠት ኺላፍ ያለበት ነጥብ አስመስሎ አቅርቦታል፡፡ ይህ ፍፁም ስህተት ነው፡፡ ምንም ኺላፍ የሌለበት አሏህና መልዕክተኛው ያረጋገጡት ሐቅ ነው፡፡ በርግጥ ይህን የሚፃረሩ የቢድዐ አራማጆች ይጠፋሉ ማለት አይደለም፡፡

[ ፀሐፊው እንዲህ አለ ☞ ለዚህም ነው የሱና አሊሞች በዚህ ዙሪያ ብዙዎቹ ዑዝር ቢልጀህል አለ ሲሉ!
 #የተወሰኑት የለም በማለት የተለያዩት። ]
ይህ ንግግሩ በሱና ዑለሞች ላይ የቀጠፈው አስቀያሚ ድፍረቱን ያሳየበት አገላለፅ ነው፡፡

•ለራሱ የስህተት መንሐጅ አሳምሮ ለማቅረብና ለመሸወድ አብዛኛው ዑለሞች በሽርክ ዑዝር ቢልጀህል አለ ይላሉ ፥ የለም የሚሉት የተወሰኑ ናቸው ማለቱ ፥ ምናልባት ዐሊም ሲባል የሚያውቀው እነዚያ የጠቀሳቸው ጥቂት ሰዎች ይሆናሉ ብዬ እጠረጥራለሁ፡፡ እንጂ በዚህ ርዕስ ዙሪያ የተፃፉ ኪታቦች ያነበበ ሰው እንዲህ አይነት የድፍረት ንግግር ሊናገር አይችልም ነበር፡፡ ሁሉም በቦታው እናየዋለን፡፡

•ማስረጃ ብሎ የጠቀሳቸው ነጥቦች ላይ ከመናገሬ በፊት ፥ አንድ በዚህ ነጥብ ላይ የሚናገር የሆነ ሰው ለይቶ ሊያውቃቸው የሚገቡ ነጥቦች አስቀምጣለሁ፡፡ እነዚህ ነጥቦች ያልተረዳ ሰው የተወናበደ እይታ ይዞ ሰዎችን ግራ ያጋባልና !! እነዚህ መግቢያዎች በትኩረት ይመልከቱ ፡፡

• እስልምና የሚያርሱና ወደክህደት የሚወስዱ ነጥቦች በሁለት ተከፍለው ሊታዩ ይችላሉ ፦
1ኛው). አንድ ጃሒል የሆነው ቢሰራው ሑጃ ሳይቆምበት የማይከፍርበት ነጥብ ነው፡፡ እነዚህ ነጥቦች ዑለማዎች መሳኢል ኸፊያ (ድብቅ የሆኑ ነጥቦች) ብለው ይጠሩታል፡፡ በዚህ የጠሩበት ምክንያት እነዚሀ ነጥቦች ማስረጃዎቻቸው አብዛኛው ሰው ዘንድ ግልፅ ያልሆኑ ስለሆኑ ሑጃ ሳይቆም በፊት በኩፍር ብይን አይሰጥም፡፡ አንዳንድ ሲፋቶች ይመሥል፥ አሏህ ሐራም ያደረገውን ሐላል ማድረግ ፥ ሃላል ያደረገውን ሐራም ማድረግ የመሳሰሉ ነጥቦች ሊካተቱ ይችላሉ፡፡

2ኛው). አንድ ጃሒል ቢሰራው ፥ ባለማወቁ ዑዝር የማይሰጥበት ነው፡፡ እሱም "ሽርክ" ነው፡፡ በአሏህ ማጋራት ዑዝር ቢልጀህል የሌለበት ከባድ ጥፋት ነው፡፡ (ኢንሻ አሏህ በማሥረጃዎች እናየዋለን፡፡)

• አል-ዑዝር በሶስት ነጥቦች ላይ ይነገራል፡፡
1). በቂያማ ቀን መቀጣት በተመለከተ ያለ ዑዝር ነው፡፡ ይህ የዒልም ፥ የመጠየቅ ዕድል ያልተመቻቸለት ሰው በጅህልናው የቂያማ ቀን አይቀጣም፡፡ ምክንያቱም አሏህ መልዕክተኛ እስከምንልክ ድረስ የምንቀጣ አይደለንም ብሏል፡፡ ማስረጃውም አሏህ እንዲህ ብሏል
وَمَا كُنَّا مُعَذِّبِينَ حَتَّىٰ نَبْعَثَ رَسُولًا، [الإسراء: 15]
  " መልዕክተኛ እስከምንልክ ድረስ የምንቀጣ አይደለንም፡፡ " አልኢስራእ፡15

° ፨ በዚህ አንቀፅ አሏህ የነገረን ሰዎቹ መልዕክተኛ መጥቶ ተጠንቀቁ ብሎ ሑጃ ሳያደርሳቸው አይቀጣቸውም ማለት እንጂ ሰዎች የሚሠሩት ሽርክ እስልምናቸው የማያፈርስ ነገር ሆኖ አይደለም፡፡ ሰዎች ተውሒዳቸው ፈርሷል፡፡ እስልምናቸው ተንዷል፡፡ ነገር ግን ይቀጡ ዘንድ መልዕክተኛ መላኩ መሥፈርት ተደርጓል፡፡

2). በዱንያ ላይ የመጋደልን ዑዝር የተመለከተ ነው፡፡ የሪዳ ሃድ በተመለከተ የሚሰጠው ዑዝር ነው፡፡ ሰዎች ሽርክ ሰራ ፥ ታድያ ቀጥታ ይገደላልን? ሑጃ አይቆምበትም? ማለት ነው፡፡ በዚህ ነጥብም ላይ ሽርክ ላይ የወደቀ ሰው አንጋደለውም ፥ የሪዳ ሃድም አይቆምበትም ሑጃ ከደረሰው በኋላ እንጂ፡፡ ነገርግን ካፊር ተብሎ ይጠራል፡፡ ሙስሊም አይደለም፡፡

3). ሽርክ ላይ የወደቀ ሰው ማክፈር እሱን ካፊር ሙሽሪክ ብሎ መጥራት በተመለከተ የሚነሳ ዑዝር ሲሆን በዚህ ላይ ሽርክ የሰራ ሰው ሑጃ ቢደርሰውም ፥ ባይደርሰውም ሙሽሪክ ተብሎ ይጠራል፡፡ ሙስሊም ነው አይባል፡፡ እንዲሁም የተክፊርን አህካሞች በሱ ላይ ይፈፀማሉ ፡፡ ነካህ አለማድረግ ፥ በሱ ላይ አለመሥገድ ፥ አለመውረስ የመሳሰሉት...

• ለዚህም ዑለማዎች ተክፊርን በሁለት እይታዎች ይገልፁታል፡፡ 1ኛው). ተክፊር ሙዐዘብ ዐለይሒ ሲሆን ..2ኛው). ተክፊር ገይረል ሙዐዘብ አለይሒ በማለት ይከፍሉታል፡፡ ብዙ ጊዜ ዐዝር ቢልጀህል አለ ብለው ማሥረጃ የሚጠቅሱ ሰዎች የቁርኣን ፥ የሃዲስ የዑለሞች ንግግር ባልፈለጉበት ቦታ በማዋል ሰዎችን ያወናብዳሉ፡፡ ይህ ፀሐፊም ይህንኑ ስህተት ደጋግሞታል፡፡ እስቲ ተክፊር ሙዐዘብ እና ገይረል ሙዐዘብ አለይሒ የሚለው ዑለሞች ተጠቅመውታል? አው፡፡ ለምሳል ኢብን ተይሚያህ ረሒመሁሏህ እንዲህ ብሏል ፦
[ والكفر المعذب عليه لا يكون إلا بعد بلوغ  الرسالة ] الفتاوى ٢/٧٨

[ አልኩፍር ሙዐዘብ (የሚያስቀጣ የሆነው ክህደት) ሪሳላ ከደረሰ በኋላ እንጂ የሚሆን አይደለም፡፡ ] አልፈታዋ፡2/78

• በዚህ ንግግሩ ከላይ እንደጠቀስኩት በአኼራም ሆነ በዱንያ ቅጣትን በተመለከተ ሑጃ ከደረሰው በኋላ እንጂ የሚሆን ነገር አይደለም፡፡ ኢብን ተይሚያም ያለው ይህንኑ ነው፡፡ ግን ሰዎች በዑለማዎች ሲቀጥፉ የአኼራን ቅጣት በተመለከተ የተናገሩት ንግግሩ ያለቦታው በማስገባት ፥ ይኸው ሼይኽ እገሌ ሽርክ ዑዝር ይሰጣሉ ተብሎ ይወራል፡፡ ግን ከዑለሞች የማስረጃ አጠቃቀም እንኳን ብናጤነው ሰውዬ በማጋራቱ ሙሽሪክ የሚል ስም ይሰጠዋል ወይስ አይሰጠውም ሳይሆን ፥ ባለማወቅ በሰራው ሽርክ ይቀጣል ወይስ አይቀጣም በሚል ዙሪያ እንደሆነ እንረዳለን፡፡

• ኢብን ተይሚያህ ፦ አንድ ሰው ሽርክ ከሰራ ሑጃ ባይደርሰውም ሙሽሪክ የሚል ስም እንደሚሰጠው ተናግሯል፡፡ እንዲህ ብሏል ፦
 إسم الشرك يثبت قبل الرسالة لأنه يشرك بربه ويعدل به ]الفتاوى ٢٠/٣٨

[ የሽርክን ስያሜ ሪሳላ ከመምጣቱም በፊት ይፀድቃል፡፡ ምክንያቱም በጌታው የሚያጋራና የሚዘነበል ስለሆነ] ብሏል፡፡ ሰዎች በሚሠሩት ሽርክ ሑጃ ቢደርሳቸውም ፥ ቢይደርሳቸውም ሙሽሪክ የሚል የሽርክ ስያሜ ይሰጣቸዋል፡፡ ግን ይቀጣሉ ወይ የሚለው ከሆኑ ሑጃ ሳይደርሳቸው አይቀጡም ነው፡፡ አሁን ማስረጃ ብሎ ያቀረባቸው እንመልከት....!!

[ መረጃ ① ብሎ ያቀረበው ]

  ﴿ وَمَنْ يُشَاقِقِ الرَّسُولَ مِنْ بَعْدِ مَا تَبَيَّنَ لَهُ الْهُدَى وَيَتَّبِعْ غَيْرَ سَبِيلِ الْمُؤْمِنِينَ نُوَلِّهِ مَا تَوَلَّى وَنُصْلِهِ جَهَنَّمَ وَسَاءَتْ مَصِيرًا ﴾.
 سورة النساء (115)

#ቅኑ መንገድ ለእርሱ ከተገለፀለት በኋላ!  መልእክተኛውን የሚፃረርና ከምእምኖቹ መንገድ ሌላ የሆነን የሚከተል ሰው በዞረበት ላይ እንተወዋለን። ጀሀነምንም እናገባዋለን።
#መመለሻይቱም ከፋች።" [ኒሳእ: 115)]

፨ ይህ አንቀፅ ሽርክ የሰራ ሰው ሙሽሪክ አይባልም የሚል ምንም አይነት ማሥረጃ የለውም፡፡ ሐቅ ከገለፀለት በኋላ መልዕክተኛው የተፃረረ ሰው ጀሀነም ይገባል ነው ጭብጡ፡፡ ሽርክ የሰራ ሰው ሙሽሪክ አይደለም ፥ ሙስለሊም ነው የሚል ትርጉም የለውም፡፡ ስለዑዝር ይጠቅሳል ቢባል እንኳን ከላይ እንዳሳለፍነው ስለ አኼራ ቅጣት እንጂ ሰውዬው በዱንያ በሰራው ሽርክ ተውሒዱ ፈርሷል ወይስ አልፈረሰም የሚል ነገር አይሰጠንም፡፡

የኢብኑ ከሲር ንግግር ብሎ የጠቀሰው ጭራሽ ከርዕሱ የማይገናኝ ሆድና ጀርባ ስለሆነ ትቼዋለሁ፡፡

[ መረጃ ② ብሎ የጠቀሰው]

 #وَمَا كُنَّا مُعَذِّبِينَ حَتَّىٰ نَبْعَثَ رَسُولًا، [الإسراء: 15]

#መልእክተኛም እስከምንልክ ድረስ የምንቀጣ አይደለንም!!
[ኢስራእ: 15]

• ከላይ እንዳሳለፍነው ይህ አንቀፅ ሽርክ ውስጥ የወደቀ ሰው ይቀጣል አይቀጣም የሚል ነጥብ ነው እንጂ በዱንያ ሙሽሪክ የሚል ስም እንሚሰጠው አያስተባብልም፡፡ ምክንያቱም አሏህ ሑጃ ያልደረሰው ሰው "ሙሽሪክ" እንደሆነ በቁርኣን አረጋግጧል፡፡ አሏህ እንዲህ አለ...
وإن أحد من المشركين إستجارك فأجره حتى يسمع كلام الله

[ከአጋሪዎችም አንዱ ጥገኝነትን ቢጠይቅ የአላህን ቃል ይሰማ ዘንድ አስጠጋው፡፡ ] በዚህ ቁርኣን አንቀፅ አሏህ ገና ሑጃ/ቁርኣን ያልሰማውን ሰው ከመሥማቱ በፊት ሙሽሪክ ብሎ ጠርቶታል፡፡ ስለዚህ ስምና አህካም መለየት ግድ ይለናል፡፡

[ ፀሐፊው እንዲህ ብሏል ☞ይህ የቁራኣን አንቀፅ መልእክተኛው ይዘውት የመጡት መልእክት የደረሰው ሰው እንጂ እንደማይቀጣ ፍንትው አድርጎ ያሳየናል።] እኛም የምንለው ቅጣት ለመቀጣት መልእክተኛ መልኩ አሏህ መሥፈርት አድርጓል፡፡ ነገርግን በዱንያ ያ ሰው ሙስሊም ነው አልተባለም፡፡

• በዚህ አንቀፅ ላይ የጠቀሳቸው ተፍሲሮች ሁሉ ትክክል ነው ግን የፀሐፊው ችግር በዚህ መስዓላ ላይ ዑለሞች { አል-አስማእ ወል-አህካም} ብለው ያብራሩት ነጥብ የተረዳው አይመሥልም፡፡ አልአስማእ የምንለው በሸሪዐ የተሰጡ ስያሜዎች ናቸው፡፡ ለምሳሌ ፦ ሙእሚን ፥ ካፊር ፥ ሙሽሪክ ፥ ሙናፊቅ ፥ ፋሲቅ ፥ ሙብተዲዕ የመሳሰሉት "አልስማእ ሸርዒያ" ናቸው፡፡ እነዚህ ስያሜዎች ተክተለው የሚመጡ "አል-አህካም" ደግሞ አሉ፡፡ ለሙእሚን መውደድ ፥ መርዳት ፥ ማገዝ ፥ ጀነት መግባት ፥ ምህረት ማግነት  ሲሆን ለካፊር ደግሞ መጥላት ፥ በራዕ ማድረግ ፥ አለመወዳጀት ፥ አለመርዳት ፥ በአኼራ እሳት መግባት የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ፡፡ እነዚህ ቀላቅሎ መጓዝ አይገባም፡፡ ኢብን ተይሚያ ረሂሐሁሏህ {አልአስማእና አልአህካም} በተመለከተ እንዲህ ብሏል ፦

[ وقد فرق الله بين ما قبل الرسالة وما بعدها في أسماء وأحكام، وجمع بينهما في أسماء وأحكام ] الفتاوى ٢٠/٣٧

" በርግጥም አሏህ ከሪሳላ በፊት ባለውና ከሪሳላ በኋላ ባለው በስምና በአህካም ላይ ለያይቷል፡፡ በነሱ መካከልም በስም ና አህካም ላይም ሰብስቧል፡፡ " አልፈታዋ፡20/37

أعلم أن مسألة التكفير والتفسيق هي من مسائل الأسماء والأحكام التي يتعلق بها الوعد والوعيد في الدار الآخرة وتتعلق بها الموالاة والمعاداة والقتل والعصمة وغير ذلك في الدنيا. /الفتاوى :٤٦٨

[ እወቅ! የተክፊር ና የተፍሲቅ ነጥብ ከስምና አህካም ጋር የሚመደብ ነው፡፡ በሱም በአኼራ ላይ ቀጠሮና ዛቻ የተያያዘበት ነጥብ ነው፡፡ በዚህ ላይ ነው ወዳጅነት ፥ ጠላትነት ፥ መገደል ፥ ደም ሐራም መሆን ሌሎችም ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ] አልፈታዋ

• እና ሁላችንም ይህ ነጥብ በደንብ መረዳት አለብን፡፡ እንዴት አድርገው የዑለሞች ንግግር ያለቦታ እንደሚያስገቡት መረዳት አለብን፡፡ እሱ ክፍል ሁለት ብሎ ያቀረባቸው ፅሁፎች በቀጣይ በክፍል አራት (4) እንመለከታለን፡፡

አሏህ ሐቅ ይግጠመን፡፡ በትክክለኛው የአንቢያዎች ዲን ላይም ይግደለን፡፡ ወሰለሏሁ ወሰለም ዐላ ነቢዪና ሙሐመድ፡፡

© ✍ አቡ ሙስሊም /ናሙስ..... ሸዕባን/1440 ዓ.ሒ

Monday, April 8, 2019

¤በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩሕሩህ እና እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው እጀምራለሁ፡፡

《ኸዋሪጅ አይደለሁም ስል በምክንያት ነው》

በመጀመርያ ምሉዕ ምስጋና ሁሉ ለአሏህ ነው፡፡ ከኃይማኖት ሁሉ መርጦ ወደኢስላም ስለመራን በድጋሚ እናመሠግነዋለን፡፡ በታላቁ ነብይ ሙሐመድ ቢን ዐብዲላህ ላይ ዘወትር የአሏህ ሰላምና ሶለት ይውረድ፡፡

¤ በኢስላም ብቅ ካሉ ትክክለኛው መንገድ ትተው በስሜትና በጥመት ወደጥፋት ከሔዱ ቡድኖች መካከል ኸዋሪጆች አንዱ ናቸው፡፡ ዘመን ዘመን እየተካ በሔደ ቁጥር ሐቅ በሰዎች ላይ በተለያየ መልኩ በባጢል እየተቀየጠ ብዙዎች ለግራ መጋባትና ዲናቸውን በትክክል ላለመረዳት ዳርጓቸዋል፡፡

¤በዚህ ፅሁፍ ላመላክት የወደድኩት ባለማወቅ ወይም ከስሜት በመነዳት የሐቅ ሰዎችን በ"ኸዋሪጅነት" የምትፈርጁ ሰዎች ቆም ብላቹ እንድታስቡና እኛም ከዚህ በባጢል ከለጠፋቹብን መጥፎ ስም የጠራን መሆናችን ታውቁ ዘንድ ነው፡፡

¤በመጀመርያ "ኸዋሪጆች" እነማን ናቸው? አጭር ገለጻ:- የዚህ ጠማማ ቡድን መጀመርያ መቼ ነበር? የዚህን መልስ በተመለከተ አልኢማም አቡበክር ሙሐመድ ቢን አልሑሰይን አል-ኣጁሪይ (360 ዓ.ሒ) ረሒመሁሏህ "አሽ-ሸሪዓህ" በተባለ ኪታባቸው ኸዋሪጆችን በተመለከተ ሲጠቅሱ እንዲህ ብለዋል ፦
فأول قرن طلع منهم على عهد رسول الله صلى الله عليه وسلم : هو رجل طعن على رسول الله صلى الله عليه وسلم ، وهو يقسم الغنائم بالجعرانة. فقال "اعدل يا محمد ، فما أراك تعدل" فقال صلى الله عليه وسلم : 《 ويلك ،فمن يعدل إذا لم أكن أعدل》
የመጀመርያ ብቅ ያሉበት ዘመን ፥ በረሱል   ዘመን ነበር፡፡

¤ እሱም አንድ ሰው ነበር ነብዩ ﷺ በጀዕራን ምርኮ እያከፋፈሉ በነበረበት ወቅት ላይ አነወራቸው (ክብራቸው ነካ)፡፡  እንዲህም አለ ፦ " አንተ ሙሐመድ ሆይ! ፍትሓዊ ሁን፡፡ ፍትሐዊ ነህ ብዬ አላይም(አላምንም)፡፡ " አላቸው፡፡ እሳቸውም እንዲህ አሉት "ወዮልህ! እኔ ፍትሐዊ ካልሆንኩ ማንነው ፍትሐዊ የሚሆነው?" አሉ፡፡

¤ ይህ አነሳሳቸው ነው፡፡ በዚህም ሐዲስ ላይ ለዚህ ክብራቸው ለነካ ሰው ባልደረቦች እንዳሉትና አንደኛቹህ ሶላቱን አሳንሶ ያያል ፥ ከዚህ ሰው አሰጋገድ ፥ ፆሙንም ከዚህ ሰው ጾም ፥ ከዲንም ተስፈንጥረው ይወጣሉ ብለዋል፡፡ ኢማም አልኣጁሪይ (360 ዓ.ሒ) እንዳሉትም እነዚህ ኸዋሪጆች ከዚያ በኋላ በተለያዩ ሐገራት ብቅ ብለዋል ይላሉ፡፡ ራሳቸውን በመልካም እንደሚያዙና ከመጥፎ እንደሚከለክሉ መሥለው ብቅ አሉ፡፡ ከዚያም መዲና መጡ፡፡ ዑስማን ቢን ዐፋን ረዲየሏሁ ዐንሁ ገደሉ፡፡ በመዲና የነበሩ የረሱል ﷺ ባልደረቦች ዑስማን ቢን ዐፋን እንዳይገደል ብዙ ጥረዋል፡፡ ግን አልቻሉም፡፡ ከዚያም በዓሊ ቢን አቡ ጧሊብ ረዲየሏሁ ዐንሁ ላይ አምፀው ወጡ፡፡ በፈረደው ፍርድ ወደው አልተቀበሉም፡፡

¤ ከዚያም "ፍርድ ሁሉ ለአሏህ ነው በማለት ፊትናቸውን አጧጧፉ፡፡ ይህ ንግግራቸው ዓሊ ቢን አቡ ጧሊብ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) " ሐቅ የሆንች ንግግር ፥ ለባጢል የተፈለገባት" ብለዋታል፡፡ እነዚህ ኸዋሪጆች ዓሊ ቢን አቡ ጧሊብ ላይ"ፍርድ ሁሉ ለአሏህ ነው" ብለው ሲያምፁ ዓሊ ቢን አቡ ጧሊብ ዛሬ እንደምናያቸው መሪዎች በሠው ሰራሽ ህግ ፈርዶ አልነበረም ፥ ወይም በዲሞቅራጢ ፈርዶ አልነበረም፡፡ እርሱ (ረዲየሏሁ ዐንሁ ) በሸሪዐ ነው የፈረደው ግን ኸዋሪጆች ስህተት በሆነ ግንዛቤ ወድቀው ነው፡፡

¤ ለመሆኑ ኸዋሪጅ አይደለሁም የምለው ?

1ኛ). ኸዋሪጆች ፦ " በሙስሊም መሪዎች ላይ አምፆ መውጣት ግዴታ ነው ይላሉ፡፡" ይህ ዐቂዳ የኸዋሪጆች ዐቂዳ ነው፡፡ እኔም ይህን እቃወማለሁ፡፡ ምክንያቱም የአሏህ መልዕክተኛﷺ እንዲህ ብለዋል ፦ ዑባዳህ ቢን ሷሚት እንዲህ ይላል ፦

دعانا رسول الله ﷺ فبايعناه فكان فيما أخذ علينا أن بايعنا على السمع والطاعة في منشطنا ومكرهنا وعسرنا ويسرنا وأثرة علينا وأن لا ننازع الأمر أهله,  قال 《الا أن تروا كفرا بواحا عندكم من الله فيه برهان》

የአሏህ መልዕክተኛ ﷺ ጠሩን፡፡ ቃልኪዳንም ተጋባናቸው፡፡ ከኛ ከያዙት ቃል መካከል በመሥማትና በመታዘዝ ላይ ነው፡፡ ደስ ባለን ጊዜም ፥ በጠላንም ጊዜ፡፡ ነገሮች በከበዱንም ጊዜ ይሁን ፥ ገር በሆነ ጊዜ፥ ችግር ቢደርስብንም የጉዳዩ ባለቤት ኃላፊነቱን እንዳንነጥቅ (ቃል ገብተናል፡፡) "የአሏህ መልዕክተኛ እንዲህ አሉ 《እናንተ ዘንድ ከአሏህ የሆነ  ማሥረጃ ያለው ግልፅ ኩፍር እስክታዩ ድረስ (ስሙ ታዘዙ፡፡》

📚ሙስሊም ፡ 1709 ዘግበውታል፡፡

¤ በዚህ መሠረት አህሉሱና ዘንድ አንድ ሙስሊም በሸሪዐ የሚያስተዳድር መሪ ግልፅ የሆነ ክህደት ካልታየበት "እሱን መጋደል አይገባም፡፡" ኸዋሪጆችም የተወቀሱት አንድ መሪ ከኢስላም የማያስወጣ ወንጀል በሠራ ጊዜ ያከፍሩታል፡፡ ሠይፍ ይዘውም ይጋደሉታል፡፡ ይህ ስህተት ነው ፡፡ ነገር ግን አንድ መሪ በሸሪዓ ማስተዳደር ትቶ በጣጉት የሚያስተዳር ከሆነ ፥ በአሏህ የሚያጋራ ከሆነ ፥ ኩፋሮችን ተወዳጅቶ ሙስሊሞች የሚጋደል ከሆነ ፥ ሌሎችም ከኢስላም የሚያስወጡ ክህደቶች የሚተገብር ከሆነ እሱን መጋደልና የሸሪዐ አስተዳደር ማምጣት የኸዋሪጆች ዐቂዳ አይደለም፡፡ ምክንያቱም የአሏህ መልዕክተኛ ﷺ መጋደል የሌለብን ኩፍር ያልሰሩ እንደሆነ ነው በማለት ለጉዳዩ ገደብ አስቀምጠዋል፡፡

¤  ኸዋሪጆች ደግሞ አምፀው የሚወጡትና የሚጋደሉት ኩፍር ያልሆኑ ወንጀሎች የሠራ ሰው ነው፡፡ ኩፍር የሰራ መሪ የሚጋደልማ "ኸዋሪጅ" በፍጹም አይባልም፡፡

¤  እዚህ ጋር መነሳት ያለበት ነጥብ ከአሏህ ውጪ ባለ ሠውሠራሽ ህግ መፍረድ ኩፍር አይደለም የሚሉ ሰዎች ሁሌም መደገፊያ የሚያደርጉት የሱረቱል ማኢዳ አንቀፅን በመጥቀስ ነው፡፡ ነገር ግን በቁርኣን ይህን ሑክም የሚያብራሩ ሌሎችም አንቀጾች አሉ በተለይ ሱረቱል ኒሳእ ፡60 ይጠቀሳል፡፡ አሏህ በዚህ አንቀፅ ከአሏህ ህግ ውጪ ያሉ ህግጋት "ጣጉት" መሆናቸው ይነግረናል፡፡

《الم ترى الى الذين يزعمون أنهم ءامنوا بمآ أنزل إليك ومآ أنزل من قبلك يريدون أن يتحاكموا إلى الطاغوت وقد أمروا أن يكفروا به》

《ወደ እነዚያ እነርሱ በአንተ ላይ በተወረደውና ከአንተ በፊትም በተወረደው አምነናል ወደሚሉት፤ አላየህምን በእርሱ እንዲክዱ በእርግጥ የታዘዙ ሲኾኑ ወደ ጣዖት መፋረድን ይፈልጋሉ፡፡ 》

¤ ይህ አንቀፅ በተመለከተ ሼይኽ ዐብድርራህማን ቢን ናሲር አስ-ሰዕዲይ እንዲህ ተርጉመውታል ፦
"يريدون أن يتحاكموا إلى الطاغوت" وهو كل من حكم بغير شرع الله فهو طاغوت.
(የሚለው) " እሱም ከአሏህ ሸሪዓ ውጪ ባለ የፈረደ ነው፡፡ እሱም ጧጉት ይባላል ይላሉ፡፡ እንደገና በእነዚህ ጧጉቶች የተፋረደን በተመለከተ እንዲህ ይላሉ ...
فكيف يجتمع هذا والإيمان ؟ فإن الإيمان يقتضي الإنقياد لشرع الله وتحكيمه في كل أمر من الأمور ، فمن زعم أنه مؤمن واختار حكم الطاغوت على حكم الله فهو كاذب في ذلك ، وهذا من إضلال الشيطان  إياهم.
《እንዴት (ወደ ጣጉት መፋረድና) ኢማን አንድ ላይ ይሰበሰባሉ? ኢማን ደግሞ ለአሏህ ሸሪዐ መታዘዝ(መጎተትን) አመላካች ነገርና በሁሉም ጉዳያችን መፋረጃ ማድረግ ነው፡፡  በአሏህ ህግ ላይ የጧጉትን ህግ መርጦ እኔ ሙእሚን ነኝ ብሎ የሞገተ እሱ በዚህ ውሸታም ነው፡፡ ይህ ከሸይጧን የሆነ ማጥመም ነው》ይላሉ፡፡

፨ ስለዚህ ወደጧጉት መፋረድና ኢማን ተፃራሪ ነገሮች ናቸው፡፡ እነዚህ በጧጉት የሚፈርዱና የተለያዩ ኩፍር ተግባራት የሚሠሩ መሪዎች መጋደል የኸዋሪጆች ዐቂዳ አይደለም፡፡ ነው የሚል ሰው ማስረጃ ማምጣት አለበት፡፡

2ኛ). ኸዋሪጆች ፦ ከባኢር(ትልልቅ ወንጀል) በተባሉ ወንጀሎች ያከፍራሉ፡፡ እኛም በፍፁም በትልልቅ ወንጀሎች አናከፍርም፡፡ እነዚህ ትልልቅ የተባሉሰ ወንጀሎች ሽርክና ከፍር ደረጃ የማያደርሱ  የሆኑ ናቸው፡፡ መስረቅ ፥ አልኮል መጠጣት ፥ ሐሜት ፥ ስዕል መሣል ፥ የመሣሰሉ ናቸው፡፡ ነገር ግን በትልቁ ሽርክና በትልቁ ኩፍር ማክፈር የኸዋሪጆች ዐቂዳ አይደለም፡፡ ምክንያቱም አሏህና መልዕክተኛው ﷺ አክፍረዋልና፡፡ ዛሬ ግን በተቃራኒው ቀብር አምላኪዎች ስታከፍር ሙስሊም አክፍረሐል ተብሎ በዚህ ወቅት "ኸዋሪጅ" የሚል ስም ይሰጡሐል ይህ ትልቅ ስህተት ነው፡፡ አንድ ቀን ኸዋሪጆች በአሏህ የሚያጋራ ሰው በማክፈራቸው ተወቅሰው አይታወቅም፡፡

3ኛው). ኸዋሪጆች በአንድ ሰው ላይ ምንዳና ቅጣት አይሰበሰብም ይላሉ፡፡ ይህ የአህሉ ሱና መንሐጅ አይደለም፡፡ በዚህም አናምንም፡፡ ኸዋሪጆች ግን አንድ ሰው ላይ ቅጣትና ጥሩ ምንዳ አይሰበሰብም ይላሉ፡፡ ይህ ስሕተት ነው፡፡

4ኛው). ኸዋዋሪጆች ዘንድ ኢማን አይበላለጥም ይላሉ፡፡ አህሉ ሱና ወል ጀመዐ ዘንድ ኢማን ይበላለጣል፡፡ ኢማን  በቀልብ የሚቋጠር ፥ በምላስ የሚነገር ፥ በአካል የሚተገበር ፥ መልካም ስራ በመሥራት ይጨምራል፡፡ አሏህን በማመፅ ይቀንሳል፡፡ ይህን የአህሉ ሱና መዝሐብ፡፡  ኸዋሪጆች ግን ይህ ጥሰው ኢማን ወጥ ነገር አድርገዋል፡፡ ስለዚህ ኸዋሪጅ አይደለንም፡፡
الإيمان قول باللسان واعتقاد بالقلب وعمل بالجوارح يزيد بطاعة وينقص بالمعصية.
5ኛው). ኸዋሪጆች ፦ ከፊል ሶሓቦችን ያከፍራሉ፡፡ ዓሊይ ፥ ጦልሓ ፥ ዓኢሻ ፥ ኢብን ዓባስ (አሏህ ስራቸው ይውደድላቸው)  ያከፍራሉ፡፡ እኛ አህሉሱና ወልጀመዐህ ከዚህ ባጢል የጠራን ነን፡፡ ዐቂዳችን ልክ ሼይኹል ኢስላም ኢብን ተይሚያህ እንደገለጸው ነው፡፡
ويقبلون ما جاء به الكتاب والسنة والإجماع من فضائلهم ومراتبهم ويفضلون من أنفق من قبل الفتح -وهو صلح الحديبية -  وقاتل، على من أنفق من بعد، وقاتل ويفضلون المهاجرون على الأنصار... (كتابه الواسطية)
《አህሉሱናዎች ፦ በቁርኣን ፥ በሐዲስ ፥ በኢጅማዕ የመጣውን ትልቅነታቸው ፥ ደረጃቸው እንቀበላለ፡፡ ከፈትሕ በፊት ከገንዘቡ የሰጠና የተጋደለ ያስበልጣሉ፡፡ ከአንሷሮች ሙሐጂሮችን ያስበልጣሉ፡፡ 》በዚህ መሠረት ሶሓቦች ላይ ባለን አቋም ከኸዋሪጆች የተለየን ነን፡፡ ሶሐቦች ሁሉንም እንወዳለን፡፡ በመካከላቸው የተፈጠረ ነገርንም አንስተን እከሌ እንዲህ ነው ፥ እከሌ እንዲህ ነው አንልም፡፡

6ኛው). ኸዋሪጆች ፦ ትልልቆ ወንጀል ለሰሩ ሙስሊሞች ሸፈዐ የለም ይላሉ፡፡ አህሉሱና ወልጀመዐ ግን ከነብያችን አስተምህሮት በመያዝ ለትልልቅ ወንጀል ባለቤቶች ሸፈዐ አለ ይላሉ፡፡ ማሥረጃቸውም የአሏህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል ፦
عن النبي ﷺ قال 《شفاعتي لأهل الكبائر من أمتي》أخرجه الترمذي
《ሸፈዐዬ ከዑመቴ ትልልቅ ወንጀል ለሰሩት ነው》ብለዋል፡፡ ስለዚህ ከኸዋሪጆች አይደለንም፡፡ እነሱ  ከባኢር የሰራ ሰው ስለሚያከፍሩ ሸፈዐ የለም ይላሉ፡፡

7ኛው). ኸዋሪጆች ፦ የአሏህ ስሞችና ባሕርያት በተመለከተ የጀሕሚዮች አቋም ያላቸው አሉ፡፡ እኛ አህሉ ሱናዎች ደግሞ ከዚህ የቢድዐ መንገድ የጠራን ነን፡፡

ومن الإيمان بالله : الإيمان بما وصف به نفسه في كتابه وبما وصف به رسوله محمد ﷺ من غير تحريف ولا تعطيل ومن غير تكييف ولا تمثيل....

" በአሏህ ከማመን መካከል :- አሏህ ራሱን በኪታቡ በገለፀበት ና መልዕክተኛ ﷺ አሏህ የገለፁበት ማመን ነው፡፡ ያለ ትርጉም ማዛባት ፥ ውድቅ ሳናደርግ ፥ ሁኔታው ሳንገልፅ ፥ ሳናመሣስል ማመን ነው፡፡" ይህ ነው የአህሉሱና ዐቂዳ ፡፡ ኸዋሪጆች ግን ይኽ ተቃርነዋል፡፡

8ኛው). ኸዋሪጆች:- ከሁለት ቅን መሪ ኹለፋዎች ራሳቸውን ያጠራሉ፡፡ ከዑስማንና ከዓሊ (ረዲየሏሁ አንሁም)
 التبروء من الخليفتين الراشدين عثمان وعلي رضي الله عنهما.
°እኛ የአህሉ ሱና ወልጀመዐ ዐቂዳ ተከታዮች ግን እንደኸዋሪጆች ዑስማንና ዓሊይ (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) አንጠላም ፡፡ እንወዳቸዋለን፡፡ በጀነት የተመሠከረላቸው እንደሆኑ እናምናለን፡፡ እናልቃቸዋለን፡፡ ኸዋሪጆች ግን እነዚህን ታላላቅ ኸሊፋዎች ይጠላሉ፡፡ እኛ በፍፁም አንጠላቸውም፡፡

9ኛው). ኸዋሪጆች ፦ ዚና የሰራ ሠው በድንጋይ ተቀጥቅጦ የሚገደልበትን የሸሪዐ ሐድ ውድቅ ያደርጋሉ፡፡
إسقاط حد الرجم عن الزاني،

°እኛ ግን ይህ በፍፁም አንልም፡፡ በረጅም እናምናለን፡፡ እንሰራበታለን፡፡

10ኛው). ኸዋሪጆች ሐይድ ያየች ሴት ሶላቷ ቀዷ ማውጣት ግዴታ ነው ይላሉ፡፡ በዚህም አጠቃላይ የሙስሊሞች ኢጅማዕ ጥሰዋል፡፡ እኛ በዚህ አናምን፡፡ ከዚህ ቆሻሻ ንግግርም የጠራን ነን፡፡
القول بوجوب قضاء الصلاة على الحائض، فخالفوا النص والإجماع .
°ጾም ነው ሸሪዐችን ቀዷ አውጡ ያለው፡፡

11ኛው). ወዘተ የተበላሸ ዐቂዳቸው ይጠቀሳል፡፡ እኛ አህሉ ሱናዎች ከዚህ ሁሉ የጠራን ነን፡፡

¤  በመጨረሻም በዚህ በሌለንበት የጥመት መንገድ በዙልም የሚፈርጀን ሁሉ  አሏህ ፊት እንጠይቀዋለን፡፡ በህይወት ኖረንም ፥ ሞተንም ከኸዋሪጅ ዐቂዳ ወደአሏህ እንጠራለን፡፡ አሏህ ሆይ! መሥክር እኛ ከኸዋሪጆች መንገድ አይደለንም፡፡

[ ወሰለሏሁ ዐለይሒ ወሰለም ወዐላ ዓሊሒ ወሰለም፡፡ ]

የኢብኑ ተይሚያህ አቋም በተሃኩም ላይ...

  ፨ በአሏህ ሥም እጅግ በጣም አዛኝና በጣም ሩህሩህ በሆነው እጀምራለሁ፡፡ ፨ በዚህ ፅሁፍ ሼይኹል ኢሥላም ኢብኑ ተይሚያህን ከኸዋሪጆች አመለካከት እናጠራለን፡፡ አቡ ኢምራን ብዙዎች እንደምታውቁት ሁለት ገሪብ የኸዋሪጆችን...