Tuesday, July 3, 2018


ሼይኽ ሱለይማን ቢን ዐብድሏህ አል-ሼይኽ (አሏህ ይዘንለት) .... እንዲህ ተጠይቀዋል ፦

፩). ለአንድ ሙስሊም ወደ ኩፋሮች ሐገር ለንግድም ይሁን ለሌላ ነገር መጓዝ ይፈቀድለታልን ??

الحمد لله ، إن كان يقدر على إظهار دينه ولا يوالي المشركين ، جاز له ذلك. فقد سافر بعض الصحابة - كأبي بكر وغيره من الصحابة - الى بلدان المشركين لأجل التجارة. ولم ينكر ذلك النبي صلى الله عليه وسلم كما رواه أحمد في مسنده وغيره.

፨ መልስ ፦ [ ለአሏህ ምስጋና ይገባው፡፡ ኃይማኖቱን ግልፅ ማድረግ የሚችል ከሆነና ፥ ሙሽሪኮችን የማይወዳጅ ከሆነ ይህ ነገር ይፈቀድለታል፡፡ ከፊል ሶሃቦች አቡበክር ይመስል ሌሎችም ሶሃቦች ለንግድ ብለው ወደ ሙሽሪኮች ሐገር ሄደዋል፡፡ ይህ ነገር ነብዩ ሰለሏሁ አለይሒ ወሰለም አልተቃወትም፡፡

- ነገር ግን ዲኑን ግልፅ ማድረግ የማይችል ከሆነና እነሱን መወዳጀት መተው የማይችል ከሆነ ወደነሱ ሐገር መሔድ አይፈቀድለትም፡፡ በነዚህ ነገር ዑለሞች መረጃ እንደጠቀሱት፡፡ ይህ ነገር የሚከለክሉ ሐዲሶች በሱ ላይ ይጠቀሳሉ፡፡]

ولأن الله تعالى أوجب على الإنسان العمل بالتوحيد، وفرض عليه عداوة المشركين.

ምክንያቱም አሏህ (ሱ.ወ) በሰው ልጆች ላይ በተውሒድ እንዲሰሩ ግዴታ አድርጓል፡፡ ሙሽሪኮችንም ጠላት አድርጎ መያዝ ግዴታ አድርጓል፡፡

ይህን ነገር ውድቅ ለማድረግ መዳረሻና ምክንያት የሆነ ነገር ሁሉ አይቻልም፡፡

እንደገና ይህ ተግባሩ እነሱ ጋር ተስማምቶ ለመሄድ ፥ ለመወደድ  ይዳርገዋል ፡፡

" ይህ በአብዛኛው ወደ ሙሽሪኮች አገር በሚጓዙ ፋሲቅ ሙስሊሞች ዘንድ የሚታየው ነው፡፡ "

📚 አልጁዩሽ አር-ረባኒያ ፡ 13-14

No comments:

Post a Comment

የኢብኑ ተይሚያህ አቋም በተሃኩም ላይ...

  ፨ በአሏህ ሥም እጅግ በጣም አዛኝና በጣም ሩህሩህ በሆነው እጀምራለሁ፡፡ ፨ በዚህ ፅሁፍ ሼይኹል ኢሥላም ኢብኑ ተይሚያህን ከኸዋሪጆች አመለካከት እናጠራለን፡፡ አቡ ኢምራን ብዙዎች እንደምታውቁት ሁለት ገሪብ የኸዋሪጆችን...