Friday, November 9, 2018

✿[ ዑዝር ቢል-ጀህል እና ማደናገሪያዎች መግለጥ ]
• ክፍል አንድ (2) ✿

💧በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህና በጣም አዛኝ በሆነው እጀምራለሁ፡፡ ከባሪያዎች ሁሉ መርጦ እስልምናን የለገሰን ፥ እንዲሁም ነብያት ሁሉ ስለተጣሩ የተውሒድ መንገድ ለገጠመን ፥ በአሏህ ከማጋራትም ለጠበቀን ፥ የአለማቱ ሁሉ ጌታና ብቸኛው ተመላኪ አሏህ ዘላለማዊ ምስጋና ለርሱ ነው፡፡

በመልዕክተኛው (ሰለሏሁ ዐለይሒ ወሰለም) ላይ እንዲሁም በባልደረቦቻቸው ፥ መንገዳቸውንም በመልካም የተከተለ ላይ የአሏህ እዝነት ፥ ሰላምና ደህንነት ዘወትር ይስፈን፡፡

ክፍል አንድ (1) ለማንበብ ይህን ሊንክ ይክፈቱ⤵️

https://abumuslim760.blogspot.com/2018/11/1.html?m=1

° ወደዋናው ነጥብ ከመግባቴ በፊት እነዚህ ነጥቦች መታወቅ አለባቸው ከሚል ነው የምጠቅሳቸው፡፡ በዚህ ፅሁፍ ከማካትተው ነጥብ አንዱ

•ሰዎች በሽርክ አልክበር ላይ ሑጃ ከመድረሱም በፊትም ሆነ ፥ በኋላ ሰውዬ ሙሽሪክ እንለዋለን ብለን ከቁርአን ፥ ከሃዲስ ማስረጃ ስናቀርብ " ይህ እኮ መጀመርያም ሙሽሪክ በነበሩት ላይ የወረደ ነው እኛ የምንለው ደሞ ሸሐደተይን መስክሮ ሳያወቅ በአሏህ ለሚያጋራ ሰው ነው፡፡ " ይላሉ፡፡ ይህ ሹብሃቸው ለመግለጥ እንሞክራለን፡፡

°[ ኢስላምና ሽርክ ሊሰበሰቡ የማይችሉ ተቃራኒ ነገሮች ]°
......................................................
•አሏህ ሱብሃነሁ ወተዐላ በቁርአኑ ፥ ነብያችን ሰለሏሁ ዐለይሒ ወሰለም በሐዲሳቸው የተለያዩ የኢስላም ሊቃውንቶች በኪታቦቻቸው የኢስላምና የሽርክ ተቃራኒነትና አንድ ላይ ሊሰበሰቡ የማይችሉ ጉዳዮች እንደሆኑ አስተምረዋል፡፡ ሐቅ አንድ ነው፡፡ የተከፋፈለ አይደለም፡፡ በአንድ ሰው ልቦና ውስጥ ሽርክና ተውሒድ በፍፁም አንድ ላይ ሊቆዩ አይችሉም፡፡

° ምክንያቱም የአንዱ መኖር ሌላውን ያፈርሰዋል፡፡ ለዚህም ነው ዑለማዎች ሁለት ተቃራኒ የሆኑ ሊሰበሰቡ የማይችሉ ነገሮች ብለው የሚገልጿቸው፡፡ አሏህ በቁርአን እንዲህ ብሏል...

فَمَاذَا بَعْدَ ٱلْحَقِّ إِلَّا ٱلضَّلَٰلُ ۖ فَأَنَّىٰ تُصْرَفُونَ

" ከእውነትም በኋላ ጥመት እንጂ ሌላ ምን አለ (ከውነት) እንዴት ትዞራላችሁ? "

° ሐቅ አንድ ብቻ ነው፡፡ ከርሱ ወዲያ ያሉ ሁሉ ባጢል ናቸው፡፡ ሰዎችም ወደአሏህ የሚወስዳቸው የሐቅ መንገድ አንድ ብቻ ነው፡፡ አሏህ በቁርአን እንዲህ ብሏል...
إِنَّا هَدَيْنَٰهُ ٱلسَّبِيلَ إِمَّا شَاكِرًۭا وَإِمَّا كَفُورًا

"እኛ ወይ አመስጋኝ ወይም ከሓዲ ሲኾን መንገዱን መራነው፤ (ገለጽንለት)፡፡"
አሏህ በቁርአን እንዲህ ብሏል...
هو الذي خلقكم فمنكم كافر ومنكم مؤمن
" እርሱ ያ ከእናንተ ከሐዲ እንዲሁም ከናንተ ሙእሚን ያለ ሲሆን የፈጠራቹ ነው፡፡ " ይለናል፡፡

° ሼይኹል ኢስላም ኢብን ተይሚያህ አሏህ ይዘንለት እንዲህ ብሏል ፦
" ለዚህም ሲባል አሏህን ያላመለከ ሁሉ ፥ ከአሏህ ውጪ ያለን ነገር የሚያመልክ ለመሆኑ ቅሮት የለውም፡፡ ከአሏህም ውጪ ያለን ነገር ያመልክና ሙሽሪክ ይሆናል፡፡ ከበኒ አደም (ከአደም ዝርያዎች) ሌላ ሶስተኛ ክፍል የለም፡፡ ወይ ሙወሒድ ነው ወይ ሙሽሪኮ ነው፡፡ ወይም ደግሞ ይኽኛው ከዚያኛው የቀላለ ነው፡፡ ልክ (ዲን) ከሚቀይሩ የተለያየ መንገድ ከሚጓዙ ነሷራዎችና እነሱ በጥመት የተመሳሰለ ራሱ ወደ ኢስላም የሚያስጠጋ ነው፡፡"

[ መጅሙዕ አልፈታዋ ፡ 14/272]

° ታላቁ ኢማም አል-ሙጀዲድ የኢማም ኢብን ዐብድልወህሃብ (ረሂመሁሏህ) የልጅ ልጅ የሆነ ዐላማህ ዐብድርራህማን ቢን ሃሰን አልሼይኽ (አሏህ ይዘንላቸው) እንዲህ ብለዋል :-

" ሽርክ የተገበረ ሰው በርግጥም ተውሒድን ትቷል፡፡ ሁለቱ ተቃራኒ ነገሮች ናቸው፡፡ አንድ ላይ ሊሰበሰቡ አይችሉም፡፡ አንዱን አንዱን የሚያፈርስ ነው፡፡ አንድ ላይ መሆን አይችሉም፡፡ ሁለቱም በአንዴ አይነሱም፡፡ "

[ አስሉል ኢስላም ወቃዒደቱሁ]

° የሽርክ መጥፎነት ፥ ቆሻሻነት ፥ አስከፊነት አንድ ሰው ቁጭ ብሎ ዐሊም ዘንድ ባይማርና ባይቀራ እንኳን ሊያውቀው የሚችል ነገር እንደሆነ የታወቀ ነው፡፡ ኢማም ኢብን አል-ቀይም (ረሂሐሁሏህ) ስለ አያቲል ሚሳቅ (ስለ ቃልኪዳኗ አንቀፅ) ሲናገሩ እንዲህ ብለዋል ፦

" ይህ የሚያመለክተው ነገር የአንድ ሰው አዕምሮው ራሱ ተውሒድን የሚያውቁበት ነው፡፡ ሽርክ ውድቅ ለመሆኑም (ዐቅል) ማስረጃ ነው፡፡ ወደዚህ ነገር መልዕክተኛ እንኳን አያስፈልጋቸውም፡፡ ይህ ደግሞ ይህን የአሏህ ቃል የሚፃረር አይደለም፡፡
"وما كنا معذبين حتى نبعث رسولا "

ይህ ነገር አፀያፊ መሆኑ ፥ ወንጀል መሆኑ ድንበር ማለፍ መሆኑ ፥ ልክ ሽርክ ራሱ ሽርክ እንደመሆኑ ነው፡፡ ሽርክ ራሱ ክልክል ከመሆኑ በፊትም ሆነ በኋላ ያው ሽርክ ነው፡፡ አፀያፊ ነገሮች ፥ ወንጀሎች ፥ መጥፎ ነገሮች እንዲህ የሆኑ ክልክል ከሆኑ በኋላ ነው የሚል ሰው ፥ ልክ ሽርክ ሽርክ የሆነ ከተከለከለ በኋላ ነው ከዚያ በፊት (ይህ ተግባር) ሽርክ አልነበረም እንደሚል ሰው ነው፡፡ እንደሚታወቀው ይህ ግልፅ የሆነ በአዕምሮም ፥ በነቅልም ኩራተኝነት ነው፡፡ "

[ መዳሪጁ አስ-ሳሊኪን ፥ 1/240]

•ነጥብ (1) :- የቁርአን አንቀፆች የሚያሰሰተላልፉት መልዕክት በወረዱበት ውስን ምክንያት ሳይሆን በሚያስተላልፉት ጥቅል መልዕክት ነው የሚታዩት፡፡

( العبرة بعموم اللفظ ليست بخصوص السبب )

• "ዋናው ነገር የቁርአን አንቀፆች በያዙት ጥቅል ንግግር እንጂ በተነገሩበት ውስን ምክንያት አይደለም የሚታዩት፡፡

فمن فعل فعل المُشركين تتناوله الآيات التي نزلت فيهم وينطبق عليه الوصف الذي وصفهم الله به .

• ሙሽሪኮች የሚሰሩትን ስራ የሰራ ሰው ፥ እነዚህ በሙሽሪኮች ላይ የወረዱ አንቀፆች ያገኙታል፡፡ እነሱን አሏህ የገለፃቸው ባህሪን በሱም ላይ ይረጋገጣል፡፡ ይህ በርካታ የዕውቀት ባለቤቶች የገለፁት ና ያስቀመጡት መርሆ ነው፡፡ ሽርክ ያው ሽርክ ነው፡፡ የሚሠራው ሰው ወይ ቦታ ወይም ዘመን ቢለያይም እንኳን፡፡

• ከዚህ የምንረዳው ነጥብ አሏህ በቁርአን የሚጠቅሳቸው አንቀፆች የሙሽሪኮችን ሁኔታና ፍርዳቸው ፥ በዛሬ ዘመን የነሱ ስራ የሚሠራ ነው በራሱ በቀጥታ ይመለከተዋል፡፡ እነዚያም ከአሏህ ውጪ ያለ ነገር ያመልኩ ነበር ፥ እነዚህም ከአሏህ ውጪ ያለን ነገር ያመልካሉ፡፡ እነዚያ ወደአሏህ ለመቃረብ ብለን ነው የሚል መከራከርያ ያመጣሉ እነዚህም አናመልካቸው ለመቃረብ ነው፡፡

• እንደው የዛሬዎቹ ከድሮዎቹ ሽርካቸውም የከፋ ነው፡፡ ልክ ሼይኹል ኢስላም ኢብን ዐብድልወህሃብ እንደገለፁት፡፡

قال شيخ الإسلام ابن تيمية رحمه الله فيمن جعل الآيات النازلة خاصة لمن نزلت بسببه ولا يشمل النوع أو المثال فقال

• ታላቁ ዐሊም ሼይኹል ኢስላም ኢብን ተይሚያህ (አሏህ ይዘንለት) እነዚህ የወረዱ አንቀፆች በነሱ ሰበብ ለወረደባቸው ሰዎች ብቻ የተወሰነ ነገር ስለሚያደርጉ ሰዎች ፥ ሌሎችን አካትትም ስለሚሉት እንዲህ ብሏል...

" አንድ ሙስሊም "ዚሃር"ን በተመለከተ የመጡ አንቀፆች ውስጥ አውስ ቢን አስሷሚት እንጂ ሌላ አይገባም ብሎ አይናገርም፡፡ የ"መራገም" አንቀፆችን ደግሞ ማንመሸ አያካትትም ዓሲም ቢን ዐዲይ እንጂ (ብሎ አንድ ሙስሊም አይናገርም) ፡፡ ኩፋሮችን የሚወቅሱ አንቀፆች የቁረይሽ ኩፋር እንጂ ሌላ አይገባም የመሳሰለው .. ይህ ሙስሊምም ሆነ አዕምሮ ያለው ሰው የሚናገረው ነገር አይደለም፡፡ "

[ መጅሙዕ አልፈታዋ ፡ 16/148]

: ( فلا يقول مسلم أن آية الظهار لم يدخل فيها إلا أوس بن الصامت وآية اللعان لم يدخل فيها إلا عاصم بن عدي وأن ذم الكفار لم يدخل فيه إلا كفار قريش ونحو ذلك مما لا يقوله مسلم ولا عاقل ) [الفتاوى 16/ 148].

• ኢማም አልሙጀዲድ አቡ ቡጠይን አን-ነጅዲይ (አሏህ ይዘንላቸው) እንዲህ ብሏል..

قال الإمام المجدد أبو بطين النجدي رحمه الله :
( أما قول من يقول أن الآيات التي نزلت بحكم المشركين الأولين فلا تتناول من فعل فعلهم فهذا كفر عظيم )

" ሙሽሪኮችን በተመለከተ የወረዱ አንቀፆች የነሱን ስራ የሰራ ሰው አያገኘውም የሚል ሰው ይህ ትልቅ የሆነ ኩፍር (ክህደት) ነው፡፡ "

، قال : ( ويلزم منه أن الحدود المذكورة في القرآن والسنة لأناس كانوا وانقرضوا ! فلا يُحد الزاني اليوم ولا تقطع يد السارق وبطل حكم القرآن ) [الدرر 10/418]

• እንዲህም ብለዋል ፦ " ይህ የሚያሲዘው በቁርአን ፥ በሃዲስ የተጠቀሱ ሓዶች (ቅጣቶች) ለነዚያ ድሮ ለጠፉት (ብቻ) ነበር ማለት ነው፡፡ ዚና የሰራ ሐድ አይቆምበትም፡ የሰረቀም እጁ አይቆረጥም፡፡ የቁርአን ሁክም ውድቅ ተደረገ ማለት ነው፡፡ "

[መጅሙዕ አልፈታዋ ፡ 10/418]

•ሼይኽ ሙሐመድ ሷሊህ አልዑሰይሚን እንዲህ ብሏል...
[ أن معنى قولنا العبرة بعموم اللفظ لا بخصوص السبب ] يعني أن الحكم لا يختص بعين الذي ورد من أحله ، وإنما يعم من كان مثل حاله. وقد نص على هذه القاعدة ابن دقيق العيد في شرح الحديث في العمدة وهو واضح.

📚 الكنز الثمين في تفسير ابن عثيمين :٥٤٤

" አልዒብራህ ቢዑሙሚ ለፍዚ ፥ ላ ቢኹሱሲ ሰበብ " የሚለው ንግግራችን ትርጉሙ ፦ ይህ ማለት አንድ ብይን (ሁክም) በዚያ በርሱ ምክንያት ለመጣበት ነገር ብቻ አይገደብም፡፡ ነገርግን የርሱን ሁኔታ የተመሳሰለ ሁሉ የሚያጠቃልል ነው፡፡ ይህን ቃዒዳ (መርሆ) በተመለከተ ኢብን ደቂቅ አልዒድ ዑምዳ ውስጥ ሐዲስ ሲያብራራ መረጃ አድርጎ ጠቅሶታል፡፡ እሱ ግልፅ ነገር ነው፡፡

[ አልከንዝ አስሰሚን ፊ ተፍሲር አልዑሰይሚን ፡ 544]

° ስለዚህ የቁርአን አንቀፆች የድሮ ሙሽሪክ ላይ የወረደ ነው ዛሬ ላሉት አይሆንም የሚለው ውድቅ የሆነ ሹብሃ ነው፡፡ የቀደምት ሙሽሪኮች ስራ የሰራ ሁሉ ያካትታል ፡፡ በዚህ በምናቀርበው ፅሁፍ በአሏህ ፍቃድ አሏህ በቁርአን በርሱ ያጋሩ ሰዎችን ዒልም ሳይኖራቸው ፥ ጃሒል ሆነው ፥ ሑጃ ሳይደርሳቸው ፥ መልዕክተኛ ሳይመጣቸው ፥ ይህ የምትሰሩት ሽርክ የሚል ሰው ሳይኖር በርሱ ያጋሩ ሰዎችን "ሙሽሪክ" ብሎ እንደጠራቸው በርካታ ማስረጃዎች እንጠቅሳለን፡፡

• ለናሙና አንድ ታላቅ ዐሊም ፈትዋ ላስነብባቹ... ይህ ዐሊም ከታላላቅ የነጅድ ዑለሞች ነበር:
🌸🍃 قال الشيخ حمد بن ناصر( من أئمة الدعوة النجدية):.

• ሼይኽ ሃምድ ቢን ናስር (ረሂመሁሏህ) ከእውቅ የነጅድ ዑለሞች ነበር፡፡ እንዲህ ብለዋል

" وأما من كان يعبد الأوثان ومات على ذلك قبل ظهور هذا الدين فهذا ظاهره الكفر وإن كان يحتمل انه لم تقم على الحجة الرسالية لجهله وعدم من ينبهه لأنا نحكم على الظاهر .

" ይህ ዲን ግልፅ ከመደረጉ በፊት ጣዕታትን የሚያመልክ የነበረና በዚህም ላይ የሞተ ሰው የዚህ ሰው ዟሂሩ (ጉልህ ፍርዱ) ክህደት ነው፡፡ ምናልባት በሱ ላይ ሑጃ ሪሳሊያህ አልቆመበትም የሚል ነገር ያሲዝ ይሆናል ፥ ጃሂል ስለሆነ ወይም የሚነግረው ሰው ስላጣ ፥ እኛ ብይን የምንሰጠው በዟሂሩ ነው፡፡

وأما الحكم على الباطن فذلك إلى الله والله تعالى لا يعذب أحدإلا بعد قيام الحجة عليه كما قال تعالى ( وما كنا معذبين حتى نبعث رسولا )

" ነገር ግን የውስጡ ፍርድ ግን ይህ ወደ አሏህ የሚመለስ ነው፡፡ አሏህ አንድንም አካል አይቀጣም ሑጃ ከቆመበት በኋላ እንጂ፡፡ ልክ አሏህ እንዳለው
( وما كنا معذبين حتى نبعث رسولا )

وأما من مات منهم مجهول الحال فهذا لا نتعرض له ولا نحكم بكفره ولا بإسلامه وليس ذلك مما كلفنا به (تلك أمة قد خلت لها ما كسبت ولكم ما كسبتم ولا تسألون عما كانوا يعملون"(الرسالة المتممة نقلا عن الدرر 10/336)

• ነገር ግን ከነሱ መካከል ሁኔታው የማይታወቅ ሆኖ የሞተ እኛ ለዚህ የምንቀርበው ነገር የለም፡፡ በኩፍርም በኢስላምም አንፈርድበትም፡፡ ይህ እኛ የተገደድንበት ነገር አይደለም፡፡
تلك أمة قد خلت لها ما كسبت ولكم ما كسبتم ولا تسألون عما كانوا يعملون"
[ አልሙተሚማህ ፥ ]

• በመጨረሻም በቀጣይ ክፍል ወደዋናው ጉዳይ ገብተን የቁርአን አንቀፅች ማስረጃ እንዘረዝራለን፡፡ አሏህ ለዚያ ያብቃን፡፡ እላለሁ፡፡ መልዕክቱ ሼር በማድረግ አስተላልፉ፡፡ አንድ ሰው ሑጃ ደርሶትም ፥ ሳይደርሰው በአሏህ ቢያጋራ ሙሽሪክ እንለዋለን፡፡ ማስረጃዎች በቀጣይ እንጠቅሳለን፡፡

° ወቢላሂ አት-ተውፊቅ....... © አቡ ሙስሊም ናሙስ

No comments:

Post a Comment

የኢብኑ ተይሚያህ አቋም በተሃኩም ላይ...

  ፨ በአሏህ ሥም እጅግ በጣም አዛኝና በጣም ሩህሩህ በሆነው እጀምራለሁ፡፡ ፨ በዚህ ፅሁፍ ሼይኹል ኢሥላም ኢብኑ ተይሚያህን ከኸዋሪጆች አመለካከት እናጠራለን፡፡ አቡ ኢምራን ብዙዎች እንደምታውቁት ሁለት ገሪብ የኸዋሪጆችን...